Telegram Group Search
#AddisAbabapolice

የሁለት ሰዎችን ህይወት አጥፍቶ የተሰወረን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፓሊስ አስታወቀ።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ህዳር 04 እና 05 ቀን 2018 ዓ/ም በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ቦታው 23 ቀበሌ መዝናናኛ ክበብ አካባቢ መሆኑን የአዲስ አበባ ፓሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።

ተከሳሽ እሱ ያውቃል ቢያዝን ከባለቤቱ ከወ/ሮ ሐመልማል አለምነህ ጋር በትዳር ተጣምረው መኖር ከጀመሩ አራት ወራትን አስቆጥረዋል፡፡

ተከሳሽ ከባለቤቱ ጋር በኪራይ ከሚኖሩበት ቤት ህዳር 04 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ ከሌላ ወንድ ጋር ስልክ ትደዋወያለሽ በሚል ቂም በቀል በመነሳሳት ሟችን አንገቷን በማነቅ ህይወቷ እንዲያልፍ በማድረግ በር ዘግቶባት ከአካባቢው ለጊዜው መሰወሩን አስረድቷል።

ተከሳሹ ከአንድ ቀን በኋላ ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ/ም ባለቤቱን ከገደለበት መኖሪያ ግቢ ተመልሶ በመምጣት ከእዚህ ቀደም ከባለቤቱ ጋር በሚፈጠረው ፀብ ያሸማግል የነበረን አለባቸው አየለ የተባለን ጎረቤቱን በሟች ባለቤቱ ይጠረጥረው ስለነበር በስምንት ጥይት ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ተሰውሯል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራና ክትትል ክፍሉ የወንጀል ስፍራው በመገኘት የሟች አለባቸው አየለን አስከሬን በማንሳትና ከአካባቢው በሰበሰበው መረጃ መነሻነት የሟች መኖሪያ ቤት ሲከፈት የሐመልማል አለምነህ አስከሬን አግኝቷል።

ተገቢውን የሰውና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በመከታተል ተጠርጣሪውን ህዳር 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን ሞላሌ ከተማ ከተደበቀበት መኖሪያ ቤት የግድያ ወንጀሉን ከፈጸመበት መሳሪያ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ መምርመራ መጀመሩንም አስታውቋል።
#AddisAbabapolice

@ThiqahETH
12😢8💔2👏1🤔1
#ስልጤ

"በእሳት አደጋው ህይወታቸውን ካጡት ሦስቱ ህፃናት ሁለቱ የ6 አመት እድሜ ያላቸው መንታያ እህትና ወንድም ሲሆኑ ሌላኛው የ2 አመት የጎረቤት ህፃን ነው" - ፓሊስ

በስልጤ ዞን ሚቶ ወረዳ በሰሶ ቆሻሜ ቀበሌ ቀጠና ሁለት ተብሎ በሚጠራው መንደር ለጊዜው መንስዔው ባልታወቀ የእሳት አደጋ የሦስት ህፃናት ህይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል።

አደጋው የደረሰው ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 10 ሰዓት 30 ገደማ መሆኑን፣ እሳቱ ደጅ ላይ ካለ ገለባ መነሳቱን፣ ህፃናቱም ገለባ ውስጥ ተኝተው እንደነበር የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጂን ሙዴ ሚሴቦ ተናግረዋል።

በአደጋው ህይወታቸውን ካጡት ሦስቱ ህፃናት ሁለቱ የስድስት አመት እድሜ ያላቸው መንታያ እህትና ወንድም ሲሆኑ ሌላኛው የሁለት አመት የጎረቤት ህፃን መሆኑ አዛዡ ተናግረዋል።

ህፃናቱ ገለባ ውስጥ መተኛታቸው ስላልታወቀ ህብረተሰቡ በእሳት የተያያዘን የቆርቆሮ ክዳን መኖሪያ ቤት ተረባርቦ ካጠፋ በኋላ ቀድሞ በእሳት የታያዘውን ገለባ ለማጥፉት ሲሞከር የህፃናቱ በድን ገላ መገኘቱንም ተናግረዋል።

አዛዡ በመጨረሻም የህፃናቱን አስክሬን ለምርመራ ወደ ሆስፒታል መላኩን ገልጸው፣ ፖሊስ የአደጋውን መንስዔ በማጣራት ላይ መሆኑን ያስታወቁ ሲሆን፣ መረጃው የወረዳውና የክልሉ ፓሊስ ነው።

@ThiqahETH
😭20😢84👏1😱1🕊1
የቀድሞዋ የአውሮፓ ህብረት የውጭ ፖሊሲ ኃላፊ ፌዴሪካ ሞገርኒ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ከአውሮፓ የውጭ እርዳታ አገልግሎት (EEAS) ለዲፕሎማቶች ስልጠና እንዲውል የተበጀተ ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው መያዛቸውን የቤልጅየም ፖሊስ አስታውቋል።

ሞገርኒ ያለመከሰስ መብታቸው ከተነሳ በኋላ የአውሮፓ የወንጀል ምርመራ ቢሮ (EPPO) የእስር ማዘዣ አውጥቶባቸዋል። #aa #brusselssignal

@ThiqahEth
3😢2
#Dessie

በደሴ ከተማ በትራፊክ አደጋ የሦስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ።

በአማራ ክልል ደሴ ከተማ ሰኞ ገበያ ክፍለ ከተማ ቢለን ተብሎ በተሰኘ ቦታ በደረሰ የመኪና አደጋ የሦስት ሰዎች ህይወት ማለፉን በከተማዋ ፖሊስ መምሪያ የ3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ፈቲያ ሀሰን ተናግረዋል።

አደጋው ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ መድረሱንም፣ አደጋው የጭነት ተሽከርካሪ መኪና በመገልበጡ ምክንያት መከሰቱን፣ በሁለትና ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።

በአደጋው በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የገለጹት ኃላፊዋ፣ የተሽከርካሪው ሹፌር በህግ ስር ሆኖ ህክምና እየተከታተለ እንደሆነና የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል። #FMC

@ThiqahEth
😭135💔3🤔2
"ሶማሊያውያንን በእኛ ሀገር ማየት አልፈልግም" - ትራምፕ

ዶናልድ ትራምፕ የሶማሊያ ዜጎችን ከአሜሪካ ለቀው እንዲወጡ አስጠነቀቁ።

ፕሬዝዳንቱ "እውነት ለመናገር በፖለቲካ ትክክል ላይሆን ይችላል፣ ግን ሶማሊያውያንን በእኛ ሀገር ማየት አልፈልግም" ሲሉ ተደምጠዋል።

"እነሱ (የሶማሊያ ዜጎች) በእኛ ሀገር ላይ የጨመሩት ነገር የለም፣ በአጋጣሚ ሀገራቸው ደግሞ ጥሩ ሁኔታ ላይ አይደለችም" ብለዋል።

የትራምፕ አስተዳደር የኢምግሬሽንና ጉምሩክ አስፈፃሚ (ICE) ቢሮ ሰነድ አልባ ሶማሊያውያን ላይ ምርመራ እንዲጀምር ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

ቢሮው በተለይ የሶማሊያ ዜጎች በስፋት ይኖሩበታል በሚባለው የሚኒሶታ ከተማ ኢላማ ማድረጋቸው ተገልጿል።  #euronews

@ThiqahETH
👏134😱4😡4🤔3🕊2
"ከአውሮፓ ጋር ወደ ጦርነት ከገባን ሩሲያ ታሸንፋለች" - ቭላድሚር ፑቲን

"ፑቲን ጦርነቱ ፍፃሜ እንዲያገኝ ይፈልጋሉ" - የትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ


ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለዩክሬን ጦርነት የአውሮፓ ሀገራትን ተጠያቂ አደረጉ።

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ እና አማቻቸው ጃሬድ ኩሽነር ሞስኮ በማቅናት ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያይተዋል።

ፑቲን በሰጡት አስተያየት "ከአውሮፓ ጋር ወደጦርነት የመግባት እቅድ የለንም፣ ከገባን ግን ሩሲያ ታሸንፋለች" ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዝዳንቱ "አንድ ጊዜ ወደ ጦርነት ከገባን የሰላም ድርድር የሚባል ነገር አይኖርም" ብለዋል።

በዊትኮፍ የሚመራው የአሜሪካ ልዑክ በበኩሉ "ከሰላም አልራቅንም" ሲል ከፑቲን ጋር የነበረው ንግግር ተስፋ ሰጭ እንደነበር አስታውቋል።

ዊትኮፍ በሰጡት መግለጫ "ፑቲን ጦርነቱ ፍፃሜ እንዲያገኝ ይፈልጋሉ" ሲሉ ተናግረዋል። #politico #timeslive

@ThiqahETH
21👏3😱1😢1😡1
የ45 እስራት የተፈረደባቸው የቀድሞው የሁንዱራንስ ፕሬዝዳንት በፕሬዝዳንት ትራምፕ ይቅርታ ከእስር ወጡ።

ፕሬዝዳንት ጁዋን ሄርናንዴዝ በአደንዛዥ እፅ እና የጦር መሳሪያ ዝውውር ወንጀል ተከሰው በአሜሪካ ታስረው ቆይተዋል።

ሄርናንዴዝ በፖሊስ የተያዙት በ2022 ሲሆን፣ ባለፈው አመት 2024 የ45 አመት እስር ተፈርዶባቸዋል።

የ57 አመቱ ጁዋን ሄርናንዴዝ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይቅርታ ተደርጎላቸው ከእስር መውጣታቸውን ባለቤታቸው አና ግራሲያ አረጋግጠዋል።

ግራሲያ "ፕሬዚዳንት ትራምፕ አዲስ ተስፋ ስለሰጡን፣ ለእውነት ስለቆሙ ምስጋና ይገባቸዋል" በማለት አመስግነዋል።   #havanatimes

@ThiqahETH
👏136🤔2
THIQAH
Photo
በእስያ የጎርፍ አደጋ 1400 ሰዎች ሲሞቱ፣ የጠፉት ቁጥር 1000 ደረሰ።

በኢንዶኔዥያ ብቻ 770 ሰዎች ሲሞቱ 463 የሚሆኑት መጥፋታቸው ተረጋግጧል።

በተመሳሳይ ሁኔታ አደጋው በበረታባት ሲሪላንካ 465 ሞት ሲመዘገብ፣ 366 ሰዎች ጠፍተዋል።

ታይላንድ በበኩሏ በአስከፊው የጎርፍ አደጋ 176 ዜጎቿ ህይወታቸው ማለፉን አስታውቃለች። #anadoluagency

@ThiqahETH
😢82💔1
THIQAH
"ሶማሊያውያንን በእኛ ሀገር ማየት አልፈልግም" - ትራምፕ ዶናልድ ትራምፕ የሶማሊያ ዜጎችን ከአሜሪካ ለቀው እንዲወጡ አስጠነቀቁ። ፕሬዝዳንቱ "እውነት ለመናገር በፖለቲካ ትክክል ላይሆን ይችላል፣ ግን ሶማሊያውያንን በእኛ ሀገር ማየት አልፈልግም" ሲሉ ተደምጠዋል። "እነሱ (የሶማሊያ ዜጎች) በእኛ ሀገር ላይ የጨመሩት ነገር የለም፣ በአጋጣሚ ሀገራቸው ደግሞ ጥሩ ሁኔታ ላይ አይደለችም" ብለዋል። የትራምፕ…
"የትራምፕ ንግግር የተሳሳተ አመለካከት ውጤት ብቻ ሳይሆን ስድብ ነው" - ሶማሊያ

ሶማሊያ በጠቅላይ ሚኒስትሯ አማካኝነት ትራምፕ ስደተኞች ላይ ያሰሙትን ንግግር ተቃወመች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ባሬ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "በሶማሊያ ዜጎች ላይ ያነጣጠረ አሉታዊ ንግግር አሰምተዋል" ብለዋል።

ባሬ "በቀላሉ ትቶ ማለፍ የተሻለ ነው" ሲሉ ተጨማሪ መረጃዎችን ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ይሁን እንጂ የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አሊ ኦማር "ሶማሊያውያን ከሚገኙበት ችግር ለማምለጥ ወይም ለመጥፋት ይጠቅማቸዋል" በማለት ተናግረዋል።

ኦማር "የትራምፕ ንግግር የተሳሳተ አመለካከት ውጤት ብቻ ሳይሆን ስድብ ነው"  ሲሉ ገልጸዋል።

ሚኒስትር ዴዔታው "ዜጎቻችን ማንነታቸውን ለዓለም ለማሳየት በትብብር መቆም አለባቸው"  በማለት አሳስበዋል። #aa

"ትራምፕ ሶማሊያውያንን በኛ ሀገር ማየት አልፈልግም" ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

@ThiqahEth
18🤔3😢1😭1
#EthiopianCoffee

ከዚህ ቀደም 9 ሺሕ ብር የነበረ የአንድ ፈረሱላ ቡና ዋጋ ወደ 20 ሺሕ ብር ናረ።

ይህን ያለው የኢትዮጵያ ቡና ማህበር፣ ላኪዎች በዚህ ዋጋ ቡና እየገዙ ለአለም ገበያ ማቅረብ እንደሚከብዳቸው፣ አርሶ አደሮች እና ላኪዎች ዋጋውን ከፍ ያደረጉት ወደፊት ይበልጥ ይጨምራል በሚል ግምት እንደሆነም ለሸገርኤፍኤም ገልጿል።

ወደ ውጪ ቡና የሚልኩ ነጋዴዎች ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች ምርቱን የሚገዙበት ዋጋ ከተወሰነ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ማህበሩ ተናግሯል፡፡

የማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ ግዛት ወርቁ እንዳሉት ቀደም ሲል በፈረሱላ 8 ሺሕ እና 9 ሺሕ ብር ከአርሶ አደሮችና አቅራቢዎች ይገዛ የነበረ ቡና አሁን በፈረሱላ እስከ 20 ሺሕ ብር ገብቷል።

ዋጋው ወደ 20 ሺሕ ብር የተደረገው ከጊዜ በኋላ ይጨምራል በሚል ቢሆንም አሁን ያለው የዓለም አቀፍ ቡና መሸጫ ግን ዋጋው እንደሚጨመር ሳይሆን እንደሚቀንስ የሚያመለክት ነው ብለዋል።

ላኪዎች ከአርሶ አደሮች እና አቅራቢዎች ቡናን የሚገዘቡት ዋጋ ካልተስተካከለ ምርቱን ለአለም ገበያ ማቅረብ አስቸጋሪ እንደሚሆን በመስጋት፣ ዋጋው አሁን ባለበት የሚቀጥል ከሆነ ኢትዮጵያ የምታገኘው ገቢ ብቻ ሳይሆን ወደ ውጪ የምትልከው ቡና መጠንም እንደሚቀንስ አቶ ግዛት ገልጸዋል። #ShegerFm

@ThiqahETH
6😢1
#Drivers

"በርካታ ሹፌሮች እና ረዳቶች ታግተው ተወስደዋል" - ማህበሩ

በአማራ ክልል ከበአዲስ ዘመን ጎንደር መንገድ ዛሬ በርካታ ሹፌሮችና ረዳቶች መታገታቸውን የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማህበር አስታውቋል።

"25/03/2018 በአማራ ክልል ከአዲስ ዘመን ጎንደር መስመር ልዩ ስሙ ፈረንጅ ውሀ ተብሎ የሚጠረው አካባቢ በርካታ ሹፌሮች እና ረዳቶች ታግተው ተወስደዋል" ብሏል ማኀበሩ።

"ይህ መስመር አጋች ዘራፊ እና ገዳይ ከመብዛቱ የተነሳ መንገዱ የሲወል መንገድ ከሆነ የቆየ ቢሆንም እስካሁን መፍትሄ አልተገኘለትም" ያለው ማህበሩ፣ "በየቦታው ለሚገደል ለሚዘረፍ እና ለሚታገት አሽከርካሪ" ፍትህ እንዲሰጥ ጠይቋል።

@ThiqahETH
11😢8🕊1
ዩናይትድ ኪንግደም በሩሲያ ተቋማት እና ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታወቀች።

ለንደን ማዕቀቡ በጂ አር ዩ የወታደራዊ ኢንተሊጀንስ ኤጀንሲ እና ማንነታቸው ባልተገለፀ የበይነ መረብ መረጃ ጠላፊ ባለሙያዎች ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ ገልፃለች።

የመረጃ ጠላፊዎቹ 29155 ያልተሳኩ የበይነመረብ ጥቃቶች ፈፅመዋል ብላለች።

ማዕቀብ የተጣለባቸው አካላት በ2018 ተመርዘው በሞቱት ሰርጌ ስክሪባል እና ዩሊያ የተባሉ አባትና ልጅ እጃቸው እንዳለበት ገልፃለች። #theinsider

@ThiqahETH
😡5👏1😱1😢1
THIQAH
"በማርበርግ በሽታ ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች አስከሬን ለቤተሰብ አይሰጥም" ተባለ አስከሬናቸው እንደማይታጠብና፣ ደህንነቱ በተጠበቀ መንገድ የቀብር ስርዓታቸው እንደማፈጸም፣ ቀብር የተፈፀመባቸው ቦታዎችም በደንብ መጠበቅ እንዳለባቸው ተገልጿል። ማህበረሰቡ የበሽታውን ከባድነት ተረድቶ ይህንን ውሳኔ መቀበል እና መተባበር አለበት ተብሏል። በሌላ በኩል ቫይረሱ በወንድ የዘር ፈሳሽ ውስጥ ለአንድ አመት ጊዜ የሚቆይ…
"የማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት" ለተጋላጭ ማህበረሰቦች ሊሰጥ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የማርበርግ ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ 5,000 የማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት ከአሜሪካ መንግስት በድጋፍ መገኘቱን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

"ክትባቱን ለኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት የአሜሪካ በኢትዮጵያ አምባሳደር አርቪን ማሲንጋ አስረክበዋል" ተብሏል።

ክትባቱ በአርማወር ሃንሰን የምርምር ተቋም በሚመራ ፈጣን የደረጃ 2 ክሊኒካዊ ሙከራ ተደርጎለት ጥቅም ላይ እንደሚውል ደግሞ፣ የጤና ሚኒስትሯ መቅደስ ዳባ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

የምርመራ ተቋሙ ከኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት ባለስልጣን ጋር በመተባበር ቁጥጥር እንደሚያደርግ፣ ክትባቱን ከህዳር 29 ቀን ጀምሮ መስጠት እንደሚጀምር፣ የጤና ባለሙያዎችንና ከፍተኛ ተጋላጭ ለሆኑ ቡድኖች በቅድሚያ እንደሚሰጥ አስረድተዋል። #MoHEthiopia

@ThiqahETH
🙏72😡1
የእስራኤል ጦር የደቡብ ሊባኖስ ነዋሪዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ።

በጅባ እና ማህሩና ከተማ የሚኖሩ ዜጎች በአስቸኳይ ለቀው እንዲወጡ መልዕክት መተላለፉን የጦሩ ቃል አቀባዩ አቢቼ አዲሬ አስታውቀዋል።

መልዕክቱ የተላለፈው የሂዝቦላ ወታደራዊ መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት ለመፈጸም በማቀድ እንደሆነ ተናገረዋል። #lbc

@ThiqahETH
7👏2🕊2😭1😡1
በእስራኤል የሚደገፈው የፍልስጤም ታጣቂ ቡድን መሪ ተገደለ።

የፖፕላር ፎርስ መሪ ያሲር አቡ ሻባብ ፀረ ሃማስ አቋም ያራምድ እንደነበር ተገልጿል።

ሻባብ ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ወደሆስፒታል ቢወሰድም በህይወት መትረፍ አልቻለም ተብሏል።

በአቡ ሻባብ ግድያ የሃማስ እጅ እንዳለበት ቢገለፅም ሀማስ የሰጠው ምላሽ የለም።

እስካሁን ድረስ ለሻባብ ግዲያ ሀላፊነት የወሰደ አካል አለመኖሩ ተገልጿል። #thejerusalempost

@ThiqahETH
👏93😢3🤔2💔2
ሩዋንዳና ኮንጎ የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ።

ትራምፕ የኮንጎ እና የሩዋንዳ መሪዎችን የሰላም ስምምነት ማፈራረማቸው ተገልጿል።

የስምምነቱ ምክንያት ኮንጎ በሩዋንዳ ድጋፍ ያገኛሉ በሚል በሚከሳቸው "የኤም23 አማፂያን" መካከል ዳግም ውጊያ ተቀስቅሶ መቆየቱ ነው።

ፕሬዚዳንት ፍሊክስ ስሼኬድ እና ፖልካ ጋሜ ለስምምነቱ በትራምፕ ግብዣ ዋሽንግተን አቅንተዋል።

ትራምፕ ከሰላም ስምምነቱ በተጨማሪ ከሀገራቱ መሪዎች ጋር የማዕድን ስምምነት ማድረጋቸው ተገልጿል።

ሩዋንዳ ለኤም 23 በድን ድጋፍ ታደርጋለች በሚል ከጎረቤቷ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ተቃርኖ ውስጥ ገብታ ቆይታለች።   #scrippsnews

@ThiqahETH
8🙏4👏1🕊1
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ህንድ ገቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ።

ሞዲ እና ፑቲን በሀገራቱ የንግድ ግንኙነት እና የዩክሬን ጦርነት ላይ መምከራቸው ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ህንድ ከሩሲያ የምትገዛውን ነዳጅ እንድታቆም እያስጠነቀቁ ባለበት ወቅት ነው ሁለቱ መሪዎች መምከራቸው የተገለጸው።

አሜሪካ ህንድ የምትፈጽመው የነዳጅ ግዥ ሩሲያ ጦርነቱን እንድትቀጥል ድጋፍ ማድረግ እንደሆነ ታምናለች ተብሏል።

@ThiqahETH
13🤔2
የትራምፕ አስተዳደር በ30 ሀገራት ላይ የጣለውን የጉዞ እገዳ ሊያራዝም መሆኑን ተገለጸ።

የአሜሪካ የሀገር ውስጥ ደህንነት ዋና ፀሐፊ ክሪስቲ ኖም ውሳኔው በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

በቀጣይ ስድስት ሌሎች ሀገራትን ጨምሮ መንግስት እገዳ የተጣለባቸውን ሀገራት ቁጥር ወደ 36 ከፍ እንደሚሉ ጠቁመዋል።

ክሪስቲ አዲስ እገዳ የሚጣልባቸው ሀገራት እነማን እንደሆኑ አልገለጹም ተብሏል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ "የውጭ  ሽብርተኝነትን ለመከላከል" በሚል 30 የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚከለክለውን ህግ ያጸደቁት የባለፈው ሰኔ ላይ ነበር።

ዋና ፀሐፊዋ ባሳለፍነው ሳምንት አንድ የአፍጋኒስታን ዜጋ ሁለት የአሜሪካ ዘብ አባላት ላይ ባደረሰው ጥቃት ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ ህጉ ይበልጥ ሊጠብቅ እንደሚችል ጠቁመዋል። #telegraph

@ThiqahETH
4🕊3👏1
በኬንያ በተከሰተው ድርቅ 2.1 ሚሊዮን ዜጎች ረሃብ ተጋርጦባቸዋል።

በሰሜን ኬንያ ዝናብ በወቅቱ ባለመጣሉ በጥቂት ወራት ውስጥ ከባድ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል ተጠቁሟል።

የሀገሪቱ ፓርላማ እና የእርዳታ ሠራተኞች ወደፊት ለሚከሰተው ረሃብ ቅድመ ዝግጅት እንድደረግ አሳስበዋል።

በአካባቢው ከባድ ሙቀት እና ከተጠበቀው በታች ዝቅተኛ ዝናብ መኖሩ ለድርቅ አደጋው መንስኤ መሆኑ ተገልጿል። 

የህንድ ውቅያኖስ ጨዋማ መሆንና የቱርካና ሀይቅ ፍሰት መቀነስ ሌላኛው ምክንያት ነው። #thestandard

@ThiqahETH
😢113🕊2😡2
THIQAH
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ህንድ ገቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ። ሞዲ እና ፑቲን በሀገራቱ የንግድ ግንኙነት እና የዩክሬን ጦርነት ላይ መምከራቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ህንድ ከሩሲያ የምትገዛውን ነዳጅ እንድታቆም እያስጠነቀቁ ባለበት ወቅት ነው ሁለቱ መሪዎች መምከራቸው የተገለጸው። አሜሪካ ህንድ የምትፈጽመው የነዳጅ ግዥ ሩሲያ…
#Update

ፑቲን እና ሞዲ የሩሲያ እና የህንድን የንግድ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ተስማሙ።

ስምምነቱ የተፈጸመው ህንድና እና ሩሲያ 23ኛ አመታዊ ጉባዔያቸውን በኒውደልሂ ባካሄዱበት ወቅት ነው።

ፕረዝዳንት ቭላድሚር ከዩክሬን ጦርነት በኋላ ወደ ህንድ ሲያቀኑ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል።

እየተገባደደ ባለው የፈረንጆቹ 2025 የሁለቱ ሀገራት የንግድ ልውውጥ 60.7 ቢሊዮን ዶላር መመዝገቡ የተመላከተ ሲሆን፣ በ2030 ይህን የንግድ ልውውጥ ወደ 100 ቢሊዮን ለማድረስ መታቀዱን መሪዎቹ አስታውቀዋል።

አሜሪካ በበኩሏ፣ ህንድ ከሩሲያ ጋር ያላትን ለአስርት አመታት የዘለቀ ግንኙነት እንድትመረምር ጠይቃለች።

ትራምፕ ከሞስኮ የነዳጅ ዘይት በመግዛት ቀዳሚ በሆነችው ኒውደልሂ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስጠንቅቀዋል።  #thewashingtontimes

@ThiqahETH
🤔42
2025/12/06 04:56:59
Back to Top
HTML Embed Code: