Telegram Group & Telegram Channel
በምዕራብ ዕዝ ቴዎድሮስ ኮር 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ ለመታደም ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ የገቡት የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሠ በበዓሉ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እኛ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የቁርጥ ቀን ልጆች እያለን ኢትዮጵያን መበተን አይቻልም፤ አይታሠብምም ብለዋል።

በውጭ ያሉ ጠላቶቻችን እና ውስጥ ያሉ ጠላቶቻችን ተሰባስበው እንመጣለን እያሉ ሲመክሩና ሲፎክሩ ይሰማል። እኛም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከመላ ህዝባችን ጋር ሆነን ምን ሊያደርጉ እንደሚመጡ ስለምናስብና ስለምናውቅ ተዘጋጅተን እንጠብቃቸዋለን፤ ያኔ የተለመደውን ዋጋ ከፍለን ኢትዮጵያን ካሰቡላት ጥፋት እንደ ትናንቱ እንታደጋለን ብለዋል።

በህጋዊ መንገድ በህዝብ የተመረጠ መንግስትን ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በአፈሙዝ ለማስወገድ የሚደረግ ማናቸውም ሙከራ ጀግናው ሠራዊታችን እያለ አይሳካም ያሉት ጄኔራል አበባው ታደሠ ለህዝብ የሚጠቅም አማራጭ ሃሳብ ያለው ማንኛውም አካል ህጋዊ እና ሠላማዊ መንገዶችን ተጠቅሞ ምኞቱን ለማሳካት መስራት እንደሚችል እና የዘመኑ ብቸኛ አማራጭም ይህ ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል።

ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ በዕለቱ ባደረጉት ንግግር 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ያከበረው የ401ኛ ቴዎድሮስ ኮር በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች የተሠጠውን ወታደራዊ ግዳጅ እንደሌሎች የጦር ክፍሎች በድል መጨረስ የቻለ መቺ የጦር ክፍል መሆኑን ተናግረዋል።

ቴዎድሮስ ኮር በሠሜኑ ህግ የማስከበር ተልዕኮ ግዳጁን በላቀ ውጤት ከፈፀመ በኋላም አሁን ተሰማርቶበት በሚገኘው የሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን፤ አሸባሪውን የሸኔን ቡድን በመምታት እና ተገዱ ወደ ሰላም እንዲገባ በማድረግ ለአካባቢው ህዝብ አንፆራዊ ሰላም ማስፈን የቻለ ኮር ነው በማለት የኮሩን የላቀ ግዳጅ አፈፆፀም ገልፀውታል።

ጄኔራል አበባው ታደሠ በመጨረሻም የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን ህዝብና አስተዳደር በአሸባሪው ሸኔ የነበረበትን ከባድ ጫና ተቋቁሞ ከሠራዊታችን ጋር በፅናት በመቆም ላሳየው ቁርጠኝነትና ለከፈለው መስዋዕትነት ሁሉ በመከላከያ ሠራዊት ስም ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

በዕለቱም ጄነራል አበባው ታደሠ እና ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አባገዳዎች እና ሃደስንቄዎች ፤ የሃገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች የተበረከተላቸውን የፈረስ ፤ ጋሻና ጦር ስጦታ ከዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ምሬሳ ፊጤ እና ከአባገዳዎች እጅ ተቀብለዋል።



group-telegram.com/NatnaelMekonnen21/45662
Create:
Last Update:

በምዕራብ ዕዝ ቴዎድሮስ ኮር 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ ለመታደም ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ የገቡት የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሠ በበዓሉ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እኛ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የቁርጥ ቀን ልጆች እያለን ኢትዮጵያን መበተን አይቻልም፤ አይታሠብምም ብለዋል።

በውጭ ያሉ ጠላቶቻችን እና ውስጥ ያሉ ጠላቶቻችን ተሰባስበው እንመጣለን እያሉ ሲመክሩና ሲፎክሩ ይሰማል። እኛም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከመላ ህዝባችን ጋር ሆነን ምን ሊያደርጉ እንደሚመጡ ስለምናስብና ስለምናውቅ ተዘጋጅተን እንጠብቃቸዋለን፤ ያኔ የተለመደውን ዋጋ ከፍለን ኢትዮጵያን ካሰቡላት ጥፋት እንደ ትናንቱ እንታደጋለን ብለዋል።

በህጋዊ መንገድ በህዝብ የተመረጠ መንግስትን ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በአፈሙዝ ለማስወገድ የሚደረግ ማናቸውም ሙከራ ጀግናው ሠራዊታችን እያለ አይሳካም ያሉት ጄኔራል አበባው ታደሠ ለህዝብ የሚጠቅም አማራጭ ሃሳብ ያለው ማንኛውም አካል ህጋዊ እና ሠላማዊ መንገዶችን ተጠቅሞ ምኞቱን ለማሳካት መስራት እንደሚችል እና የዘመኑ ብቸኛ አማራጭም ይህ ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል።

ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ በዕለቱ ባደረጉት ንግግር 4ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ያከበረው የ401ኛ ቴዎድሮስ ኮር በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች የተሠጠውን ወታደራዊ ግዳጅ እንደሌሎች የጦር ክፍሎች በድል መጨረስ የቻለ መቺ የጦር ክፍል መሆኑን ተናግረዋል።

ቴዎድሮስ ኮር በሠሜኑ ህግ የማስከበር ተልዕኮ ግዳጁን በላቀ ውጤት ከፈፀመ በኋላም አሁን ተሰማርቶበት በሚገኘው የሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን፤ አሸባሪውን የሸኔን ቡድን በመምታት እና ተገዱ ወደ ሰላም እንዲገባ በማድረግ ለአካባቢው ህዝብ አንፆራዊ ሰላም ማስፈን የቻለ ኮር ነው በማለት የኮሩን የላቀ ግዳጅ አፈፆፀም ገልፀውታል።

ጄኔራል አበባው ታደሠ በመጨረሻም የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን ህዝብና አስተዳደር በአሸባሪው ሸኔ የነበረበትን ከባድ ጫና ተቋቁሞ ከሠራዊታችን ጋር በፅናት በመቆም ላሳየው ቁርጠኝነትና ለከፈለው መስዋዕትነት ሁሉ በመከላከያ ሠራዊት ስም ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

በዕለቱም ጄነራል አበባው ታደሠ እና ጄኔራል ጌታቸው ጉዲና የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አባገዳዎች እና ሃደስንቄዎች ፤ የሃገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች የተበረከተላቸውን የፈረስ ፤ ጋሻና ጦር ስጦታ ከዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ምሬሳ ፊጤ እና ከአባገዳዎች እጅ ተቀብለዋል።

BY Natnael Mekonnen












Share with your friend now:
group-telegram.com/NatnaelMekonnen21/45662

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

There was another possible development: Reuters also reported that Ukraine said that Belarus could soon join the invasion of Ukraine. However, the AFP, citing a Pentagon official, said the U.S. hasn’t yet seen evidence that Belarusian troops are in Ukraine. The Russian invasion of Ukraine has been a driving force in markets for the past few weeks. Some privacy experts say Telegram is not secure enough Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender. Ukrainian forces have since put up a strong resistance to the Russian troops amid the war that has left hundreds of Ukrainian civilians, including children, dead, according to the United Nations. Ukrainian and international officials have accused Russia of targeting civilian populations with shelling and bombardments.
from no


Telegram Natnael Mekonnen
FROM American