Telegram Group Search
#MoE

በሰኔ 2017 የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና #ዳግም ለመፈተን እየተጠባበቁ ያሉ አመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ሚያዝያ 14 /2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 05/2017 ዓ.ም የሚከናወን መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

የመመዝገቢያ ቅፅ https://exam.ethernet.edu.et ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ቀን ወደፊት ይገለፃል ተብሏል፡፡

ፈተናውን ለመውሰድ የብሔራዊ (ፋይዳ) መታወቂያ መያዝ ግዴታ ሲሆን ፤ የአገልግሎት ክፍያ (500 ብር) በቴሌብር በኩል ብቻ የሚፈፀም መሆኑ ተገልጿል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍4
ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ሥራ በይፋ አስጀምረናል- አቶ አረጋ ከበደ

የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም አካል የሆነውን ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ሥራ በይፋ አስጀምረናል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አስታወቁ፡፡

ርዕሰ መሥተዳድሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ፤ ዛሬ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ማስፈጸሚያ ዕቅድን ከአሥተዳደር ምክር ቤት አባላት ጋር ገምግመናል ብለዋል።

የሪፎርም ሂደቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ መሆኑን አረጋግጠናል ያሉት አቶ አረጋ፤ የሪፎሩሙ አካል የሆነውን ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ሥራም በይፋ አስጀምረናል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ለሕዝባችን ዘላቂ ልማት እና ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚተጋ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት የሪፎርም ሥራውን ከፍ ባለ ቁርጠኝነት ለመፈፀም እንሠራለን ብለዋል፡፡

#FMC
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
😁31👍1
የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ውጤት መቼ ይገለጻል?

የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና (EHPLE) ከሚያዝያ 1-4/2017 ዓ.ም መሰጠቱ ይታወቃል።

ውጤት መቼ ይገለጻል የሚሉ በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል፡፡

ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊ የጠየቅን ሲሆን፤ ተከታዩን ምላሽ አድርሰውናል፦

"ጤና ሚኒስቴር የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ውጤትን ለማሳወቅ እየሠራ ይገኛል፡፡ ሚኒስቴሩ የሚከተለው የ EHPLE ፕሮቶኮል፥ ፈተናው ከተጠናቀቀ በኋላ ባሉት 45 ቀናት ውስጥ ውጤት ይፋ መደረግ እንዳለበት ያስገድዳል፡፡ በዚህ መመሪያ መሰረት ውጤት ለማሳወቅ እየተሠራ ይገኛል፡፡"

ውጤት ይፋ እስከሚያደርግ በትዕግስት እንድትጠብቁ እንጠይቃለን፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍3
#Reminder

የፋይዳ መታወቂያ አውጥተዋል?

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ተፈታኞች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ሊያወጡ እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

የመንግሥት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባውን በጊዜ በማድረግ የፋይዳ መታወቂያዎን ይያዙ።


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍103
ፓስፖርት ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያን እንደ ቅድመ ሁኔታ የሚጠይቅ አሰራር ተግባራዊ ሊደረግ ነው

ከሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ፓስፖርት ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያን እንደ ቅድመ ሁኔታ የሚጠይቅ አሰራር ተግባራዊ እንደሚደረግ፤ የኢምግሬሽን ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል።

አገልግሎቱን ለማስጀመር የእቅድ ዝግጅት እና የቅድመ-ትግበራ ሥራዎች መጀመራቸውም፤ በዛሬው ዕለት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተብራርቷል፡፡

የአሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር በዛሬው ዕለት በጋራ በሰጡት መግለጫ እንደተባለው፤ የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ከሚያስፈልጉ ሰነዶች መካከል የፋይዳ መታወቂያ አንዱ እንዲሆን ከስምምነት ላይ ተደርሷል።

ይህ የጋራ ትግበራ ማንነትን በማጭበርበር የተለያዩ ሰነዶችን ለማግኘት የሚጥሩ ወንጀለኞችን ተግባር እንደሚገታም በመግለጫው ተጠቅሷል። 

በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የፓስፖርት አገልግሎት ጥያቄ አቅርበው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ግለሰቦች የተዘጋጀላቸውን ፓስፖርት ሲቀበሉ በቅድሚያ በፋይዳ ተመዝግበው ልዩ ቁጥር ሊኖራቸው እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፤ "ተገልጋዮች የፋይዳ መታወቂያቸውን በወረቀት ወይም በዲጅታል በማሳየት አገልግሎቱን ያገኛሉ" ተብሏል፡፡

የተቋሙ አገልግሎት ሰጪዎች የቀረበላቸውን በህትመት ወይም 'በሶፍት ኮፒ' የፋይዳ መታወቂያ ትክክለኛነት በመተግበሪያ አረጋግጠው አገልግሎት እንደሚሰጡም ተጠቅሷል፡፡ 

በዚህ የጋራ ትግበራ በቀጣይ የፋይዳ መታወቂያን በአገልግሎቱ ከሚለሙ ስርዓቶች ጋር በማስተሳሰር፤ የፋይዳ ስርዓትን ከሲቪል እና የቤተሰብ ምዝገባ ስርዓት፣ ከመኖሪያ ፍቃድ ስርዓት እና ከትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ስርዓት ጋር ለማስተሳሰር እንዲቻል የማድረግ እቅድ እንዳላቸውም ተቋማቱ አስታውቀዋል፡፡


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍71
ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ የሚያደርግ ሕግ ሊተገብር መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

ሕጉን ወደ መሬት ለማውረድ ትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች እና ከዘርፉ አመራሮች ጋር ውይይት ለማድረግ ዕቅድ ይዟል፡፡

በሕጉ ዙሪያ ሸገር ኤፍኤም ያነጋገራቸው መምህራን ውሳኔው ጥሩ መሆኑን ገልፀው፤ ሊታዩ የሚገባቸው ሌሎች ነገሮች መኖራቸውን አንስተዋል፡፡

ተማሪዎች አሁን ላይ ክፍል ውስጥ ሞባይል ስልክ ይዘው ሲማሩ ‘’ትምህርታቸው ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ፣ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን መከታተል እንደሚያበዙ" ጠቅሰዋል፡፡

ስልክ መያዛቸው ከትምህርታቸው እንዲናጠቡ እያደረጋቸው መሆኑን ያነሱት መምህራኑ፤ መፅሐፍት እና ጥናት ላይ ከማተኮር ይልቅ ሌሎች ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂዎች ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ አድርጓል ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ትምህርት ቤቶች ሊያሟሏቸው የሚገቡ ጉዳዮች እንዳሉ ገልፀዋል፡፡ በቂ የመፅሐፍት አቅርቦት፣ የICT ላብ፣ የኮምፒውተር ግብዓቶች እንዲሁም የተለያዩ አጋዥ መፅሐፍት ሊሟሉ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍62
የፈተና ጊዜ ተውቋል!!

በኦሮሚያ ክልል የ 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከ ሰኔ 03-05 2017 ይሰጣል ።

የ6ኛ ክፈል ክልላዊ ፈተና ደግሞ ግንቦት 26-27 እንደሚሰጥ ተብሏል ።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍7
Forwarded from In Africa Together
🌏IAT & IAIC INTERNATIONAL STUDENT FAIR🌎

Ready to study abroad and change your life?

🎓This is your chance to meet top university representatives from:

USA 🇺🇸 Canada 🇨🇦 Sweden 🇸🇪
Germany 🇩🇪 France 🇫🇷 Finland 🇫🇮 Denmark 🇩🇰 and more!

📆 May 3 & 4
🕐 3:00 - 10:00 (LT)
📍Ghion Hotel

Don’t forget to bring:
🪪Passport or Birth certificate
📚Transcripts or Student copy

Entrance Fee: FREE!!

💡Opportunities:
- Study loan options
- Learn about the scholarships offered

🏆Don’t miss this golden opportunity to take your future global!

🆓No entrance fee — just register now!

Click the link below to book your spot: 🔗
https://forms.gle/81ZueGK5d9R9Cg9P6
3👍1
#ExitExam

"pass እና fail መውጫ ፈተና 👉ለወደቁ ብቻ ነው"

የኢትዮጵያ  ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ፅ/ቤት መልዕክት 👇

1.ይህ ከላይ ተያይዞ ያለው  የተፃፈው በክቡር አቶ ኮራ ጡሸኔ ሚኒሰትር ደኤታ ሲሆን ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት ቀደም ብለን ስለ exit exam የወደቁ ማለትም ማለፍያ ነጥብ ያላመጡ ተማሪዎች  በሚመለከት ቆይታ አድርገን እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። በዚህም መመርያ ወጥቶበት በነበረው መሠረት የወደቁትን ተማሪዎች special diploma ተብሎ ይሰጣል በዚሁ መሠረት ብዙ ተማሪዎች ግራ ተጋብታቹህ ነበር ይህ certificate format ላልወደቁ ተማሪዎች ያካትታል ወይስ አያካትትም እና ለምንስ pass ይላል የሚሉ ጥያቄዎች በስፋት ተጠይቋል። እናም ይህ ለወደቁት ተማሪዎች ብቻ የሚመለከት እንጂ መውጫ ፈተና ማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች #አይመለከትም ያለፉ ተማሪዎች በነበረው ይቀጥላል ።

2. ከዛሬ አመት ጀምሮ ማንም ዩኒቨርስቲ የሞዴል ፈተና ለተማሪዎቹ እንዲፈተኑ ያደርጋል።

3. የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች exit exam ውጤት  የተሰዘረዘባቸውም በጥልቀት ተወያይተናል::

4.የመውጫ ፈተና በሰዓቱ በተያዘለት ፕሮግራም ይሰጣል  ዝግጅትም እየተደረገ ነው::

5.የNGAT ዝግጅት ላይ ነው::

6. በተለያዩ ምክንያት በሰሜኑ ጦርነት የትምህርታቸው ውጤት እንዲላክ ቀዳሚ አድርገን እየሰራን ነው::

7.ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ከሁሉም ዩኒቨርስቲ የስራ እና ፈጠራ ክህሎት እንዲኖረው እየሰራን እንገኛለን።

8. ጠንካራ አደራጃጀት በመቅረፅ ተማሪዎች እናገለግላለን።

9. አንድ ተማሪ አንድ ድግሪ ብቻ ይዞ እንዳይወጣ ሌላ online   ትምህርቶቹም ተምረው ድግሪ የሚይዙበት ፕሮግራም እየቀረፅን ነው።


የኢትዮጵያ  ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ፅ/ቤት

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍182
የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በሰላም በር እቅመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2ኛ ክፍለ ተማሪን የቤት ስራ አልሰራሽም በማለት ተገቢ ያልሆነ ቅጣት በፈጸመችው መምህርት ላይ እርምጃ መውሰዱን አሳወቀ

የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በሰላም በር እቅመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2ኛ ክፍለ ተማሪን የቤት ስራ አልሰራሽም በማለት ከእውቀት እናት የማይጠበቅ ተገቢ ያልሆነ ቅጣት በፈጸመችው መምህርት ላይ ጉዳዩን በማጣራት ከስራ በማገድ በህግ ጥላ ስር እንድትሆን ማድረጉን አስታውቋል።

ትውልድን ከመቅረፅ፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ተተኪ ዜጋን ከመፍጠርና የቀለም እናት ከመሆን ባለፈ ከእናት የማይጠበቅ ፤ ያለንበትን ዘመንና ወቅት የማይዋጅና የማይመጥን መሰል ድርጊት መፈጸም ተገቢ አለመሆኑን የገለፀው ቢሮው ድርጊቱ እንደተፈጸመ ጥብቅ ክትትል በማድረግ ወዲያዉኑ የማጣራት ስራዎች እንዲሰሩና መምህርቷ በህግ ከለላ ውስጥ እንድትሆን ማድረጉንና ጉዳዩም በህግ አግባብ እንዲታይና ፍትህ እንዲያገኝ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡

ጉዳቱ የደረሰባት ተማሪም ህክምና አግኝታ በጥሩ የጤንነት ሁኔታ ላይ የምትገኝ ሲሆን በነገው እለትም ትምህርቷን የምትጀምር ይሆናል ብሏል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ መሰል ችግሮች እንዳይፈጸሙና ለሌሎችም ትምህርት እንዲሆን ይህንን እርምጃ የወሰደ መሆኑን ገልፆ በህግ አግባብ የሚሰጠዉን ውሳኔም ተከታትሎ በቀጣይ የሚያሳውቅ መሆኑንም እምሳውቋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍21😢72😱2
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ዓመት በኑክሌር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት መስጠት ይጀምራል።

እ.አ.አ. በ2026 ከ2ዐ እስከ 25 ተማሪዎች ተቀብሎ ማስተማር እንደሚጀምር ዩኒቨርስቲው ገልጿል።

ለዚህም ዩኒቨርሲቲው ከቻይናው ሽንግዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን የካሪኩለም ቀረጻ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የአፍሪካ ኑክሌር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል እንዲሆን መመረጡን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ከዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ እና የቻይናው ሽንግዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስር የአፍሪካ ኑክሌር ሳይንስ ማዕከል እንዲቋቋም ስምምነት ተደርጓል፡፡

ማዕከሉ ከኢትዮጵያ ባለፈ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የሚመጡ ተማሪዎች የሚቀበል መሆኑ ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው አምስት ኢትዮጵያውያንን ወደ ሩሲያ እና ቻይና በመላክ በኑክሌር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በመጀመርያ ዲግሪ ሥልጠና ላይ መሆናቸውንና የመጨረሻ ዓመት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡

የኑክሌር ሳይንስ ቴክኖሎጂ ማዕከሉን ሥራ ለማስጀመር ብቻ 200 ሚሊዮን ብር ይፈጃል የተባለ ሲሆን፤ ወጪውን ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ እንደሚሸፍን ተገልጿል፡፡ #ሪፖርተር

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍105
❗️አርምጃ ይወሰድባቸዋል

በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከ25 በመቶ በታች ውጤት በሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እርምጃ እንደሚመወሰድ ተገለፀ።

ይህ የተገለጸው የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ውጤት ከ25 በመቶ በታች የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል እርምጃ እንደሚወሰድ አመላክተዋል።

የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በብቃትና በችሎታ እንዲመደቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተው " አሰራራቸውን ለማዘመንም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ማሰልጠኛ ተቋም ለማቋቋሞ እየተሠራ ነው " ብለዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
https://www.group-telegram.com/temhert_bebete.com
👍31
2025/08/20 18:22:14
Back to Top
HTML Embed Code: