🌹🌹🌹ማህሌተ ፅጌ🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
ሁለተኛ ሳምንት ማህሌተ ፅጌ በእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ይህን ይመስል ነበር።
ጥቅምት 9 2018 ዓ.ም
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
ሁለተኛ ሳምንት ማህሌተ ፅጌ በእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ይህን ይመስል ነበር።
ጥቅምት 9 2018 ዓ.ም
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
❤2
✨🌹ይእቲ ተዓቢ እምአንስት እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት መድኃኒቶሙ ለነገሥት አክሊል ንጹሕ ለካህናት ብርሃኖሙ ለከዋክብት✨🌹
✨🌹ከሴቶች ይልቅ ከፍ ከፍ ትላለች ፡፡ የሰማዕታት እናታቸው ነች ፡፡ የመላእክት እኅታቸው ነች ፡፡ የነገሥታት መድኃኒታቸው ነች ፡፡ ለካህናት ንጹሕ አክሊላቸው ነች ፡፡ የከዋክብት ብርሃናቸው ነች ፡፡✨🌹
✨🌹ከሴቶች ይልቅ ከፍ ከፍ ትላለች ፡፡ የሰማዕታት እናታቸው ነች ፡፡ የመላእክት እኅታቸው ነች ፡፡ የነገሥታት መድኃኒታቸው ነች ፡፡ ለካህናት ንጹሕ አክሊላቸው ነች ፡፡ የከዋክብት ብርሃናቸው ነች ፡፡✨🌹
❤8👏1
+• ልብ የሚዘልቁት የቅዱስ ኤፍሬም ጸሎቶች •+
ጸሎቶቻችን ሁሉ በምድራዊ ነገሮች ታጥረው እየተጉተመተሙ ለሚቀሩብን ከንቱ ለምንሆን ለእኛ የትሑቱ ቅዱስ ኤፍሬም ጸሎቶች እጅጉን አስተማሪ ናቸው:: በዚህ ተርጉሜ ያቀረብኳቸው ሁለት ጸሎቶች የሁላችንን ጸሎት ሰማያዊ በሆነው ቅኝት ያስተካክሉልን ዘንድ ተስፋ አደርጋለሁ:: ቅዱስ ኤፍሬም ስለ ምን እንደሚጸልይ ልብ እንበል:: ጸሎቱን እንጸልየው፤ የራሳችንንም ጸሎት እንቃኝበት::
+•ጸሎት አንድ•+
አቤቱ አምላኬ፤ የሕይወቴ ጌታ፤ በስንፍና እና በተመራማሪነት መንፈስ፤ እንዲያውም በመላቅ ምኞት እና በከንቱ ልፍለፋ መንፈስ እንዳልበከል ፈቃድህ ይሁንልኝ::
ከዚህ ይልቅ ለእኔ ለአገልጋይህ የንጽሕና እና የትሕትናን መንፈስ፤ እንዲያውም የትእግስትን እና ባልንጀራን የመውደድን መንፈስ ስጠኝ::
አቤቱ ጌታዬና ንጉሤ ሆይ፤ ለባልንጀሮቼ ክፉ ያለማሰብን እና የራሴን ኃጢአቶች የማየትን ጸጋ ስጠኝ::
አንተ ብጹዕ ነህና፤ ዛሬም ዘወትርም፤ ለዘለዓለሙ አሜን::
+• ጸሎት ሁለት •+
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ በሕይወትም ሆነ በሞት ላይ አንተ ኃያል ነህ:: ምስጢር የሆነውንና የተደበቀውን አንተ ታውቃለህ፤ አሳቦቻችንም ሆነ ስሜቶቻችን ከአንተ የተሸሸጉ አይደሉም::
ከምንታዌነት ፈውሰኝ፤ እኔ በአንተ ፊት ክፉ አድርጌያለሁ:: አሁን ሕያው መሆኔ እለት ከእለት ስትቀንስ፤ ኃጢአቶቼ ደግሞ ይጨምራሉ::
አቤቱ ጌታ፣ አምላከ ሥጋ ወነፍስ፣ የሥጋዬንም ሆነ የነፍሴን እጅግ ደካማ መሆን አንተ ታውቃለህ::
አቤቱ ጌታዬ፤ በድካሜ ውስጥ ጉልበትን ስጠኝ፣ በሐዘኔም ውስጥ አጽናኝ:: በቸርነት የላቅህ ጌታ ሆይ፤ አንተ ያደረግህልኝን ማሰብ እንዳልተው አመስጋኝ ነፍስን ስጠኝ:: በደሎቼን ሁሉ ይቅር በለኝ እንጂ ብዙ የሆኑትን ኃጢአቶቼን አታስብብኝ::
አቤቱ ጌታዬ፤ የኔ የክፉውን ኃጢአተኛ ጸሎት አትናቀው:: ከዚህ በፊት እንደጠበቀኝ ሁሉ ለወደፊትም እንዲጠብቀኝ በጸጋህ እስከመጨረሻው አጽናኝ:: ጥበብን ያስተማረኝ ያንተ ጸጋ ነው፤ የእርሷን [የጥበብን] መንገድ የሚከተሉ ብጹዓን ናቸው፤ የክብር አክሊልን ይቀዳጃሉና::
አቤቱ ጌታ ሆይ፤ ምንም የማልረባ ብሆንም ስንኳ አመሰግንሃለሁ፤ አከብርሃለውም፤ ለእኔ ያለህ ምህረት ገደብ የለውምና:: ረዳቴና ጠባቂዬ አንተ ነህ:: የግርማዊነት ስምህ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁን::
ለአንተ ለአምላካችን ምስጋና ይሁን::
አሜን::
🖋 Fresenbet G.Y Adhanom
ጥቅምት 9 2018 ዓ.ም
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
ጸሎቶቻችን ሁሉ በምድራዊ ነገሮች ታጥረው እየተጉተመተሙ ለሚቀሩብን ከንቱ ለምንሆን ለእኛ የትሑቱ ቅዱስ ኤፍሬም ጸሎቶች እጅጉን አስተማሪ ናቸው:: በዚህ ተርጉሜ ያቀረብኳቸው ሁለት ጸሎቶች የሁላችንን ጸሎት ሰማያዊ በሆነው ቅኝት ያስተካክሉልን ዘንድ ተስፋ አደርጋለሁ:: ቅዱስ ኤፍሬም ስለ ምን እንደሚጸልይ ልብ እንበል:: ጸሎቱን እንጸልየው፤ የራሳችንንም ጸሎት እንቃኝበት::
+•ጸሎት አንድ•+
አቤቱ አምላኬ፤ የሕይወቴ ጌታ፤ በስንፍና እና በተመራማሪነት መንፈስ፤ እንዲያውም በመላቅ ምኞት እና በከንቱ ልፍለፋ መንፈስ እንዳልበከል ፈቃድህ ይሁንልኝ::
ከዚህ ይልቅ ለእኔ ለአገልጋይህ የንጽሕና እና የትሕትናን መንፈስ፤ እንዲያውም የትእግስትን እና ባልንጀራን የመውደድን መንፈስ ስጠኝ::
አቤቱ ጌታዬና ንጉሤ ሆይ፤ ለባልንጀሮቼ ክፉ ያለማሰብን እና የራሴን ኃጢአቶች የማየትን ጸጋ ስጠኝ::
አንተ ብጹዕ ነህና፤ ዛሬም ዘወትርም፤ ለዘለዓለሙ አሜን::
+• ጸሎት ሁለት •+
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ በሕይወትም ሆነ በሞት ላይ አንተ ኃያል ነህ:: ምስጢር የሆነውንና የተደበቀውን አንተ ታውቃለህ፤ አሳቦቻችንም ሆነ ስሜቶቻችን ከአንተ የተሸሸጉ አይደሉም::
ከምንታዌነት ፈውሰኝ፤ እኔ በአንተ ፊት ክፉ አድርጌያለሁ:: አሁን ሕያው መሆኔ እለት ከእለት ስትቀንስ፤ ኃጢአቶቼ ደግሞ ይጨምራሉ::
አቤቱ ጌታ፣ አምላከ ሥጋ ወነፍስ፣ የሥጋዬንም ሆነ የነፍሴን እጅግ ደካማ መሆን አንተ ታውቃለህ::
አቤቱ ጌታዬ፤ በድካሜ ውስጥ ጉልበትን ስጠኝ፣ በሐዘኔም ውስጥ አጽናኝ:: በቸርነት የላቅህ ጌታ ሆይ፤ አንተ ያደረግህልኝን ማሰብ እንዳልተው አመስጋኝ ነፍስን ስጠኝ:: በደሎቼን ሁሉ ይቅር በለኝ እንጂ ብዙ የሆኑትን ኃጢአቶቼን አታስብብኝ::
አቤቱ ጌታዬ፤ የኔ የክፉውን ኃጢአተኛ ጸሎት አትናቀው:: ከዚህ በፊት እንደጠበቀኝ ሁሉ ለወደፊትም እንዲጠብቀኝ በጸጋህ እስከመጨረሻው አጽናኝ:: ጥበብን ያስተማረኝ ያንተ ጸጋ ነው፤ የእርሷን [የጥበብን] መንገድ የሚከተሉ ብጹዓን ናቸው፤ የክብር አክሊልን ይቀዳጃሉና::
አቤቱ ጌታ ሆይ፤ ምንም የማልረባ ብሆንም ስንኳ አመሰግንሃለሁ፤ አከብርሃለውም፤ ለእኔ ያለህ ምህረት ገደብ የለውምና:: ረዳቴና ጠባቂዬ አንተ ነህ:: የግርማዊነት ስምህ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁን::
ለአንተ ለአምላካችን ምስጋና ይሁን::
አሜን::
🖋 Fresenbet G.Y Adhanom
ጥቅምት 9 2018 ዓ.ም
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
❤3
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
✞✞✞ ጥቅምት 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞
✞✞✞ አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ ✞✞✞
✞✞✞ በሃገራችን ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ እኒህ ጻድቅ ናቸው:: ጻድቁ የተወለዱት በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን አጋማሽ ኣካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅና ቅድስት እድና ይባላሉ:: የተለወለዱበት አካባቢም ሮም ነው::
+ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው:: ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረ አምላክ ተብለዋል:: በኢትዮዽያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ::
+በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል:: ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር 7 ያህል የቤተ መንግስት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል::
+"የት ልሒድ" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮዽያን አሳያቸው:: ተመልሰውም ለ8 ባልንጀሮቻቸው "ሃገርስ ባሳየሁዋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር" ብለው ከ8ቱ ጋር ወደ ኢትዮዽያ መጡ::
+በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ:: ወደ ሃገራችን የመጡ በ470ዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል:: በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጻሕፍትን እየተረጐሙ: ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል::
+ለሥራ በተለያዩ ጊዜም አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ብዙ ደክመዋል:: በመጨረሻ ግን ደብረ ዳሞን (ደብረ ሃሌ ሉያን) አይተው ወደዷት:: የሚወጡበት ቢያጡም ጅራቱ 60 ክንድ የሚያህል ዘንዶ ተሸክሞ ከላይ አድርሷቸዋል::
+እንደ ወጡም "ሃሌ ሉያ ለአብ: ሃሌ ሉያ ለወልድ: ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ" ብለው ቢያመሰግኑ ከሰማይ ሕብስት ወርዶላቸው ተመግበዋል:: በዚህም ቦታዋ "ደብረ ሃሌ ሉያ" ተብላለች:: ጻድቁ ቦታውን ከገደሙ በኋላ ከተለያየ ቦታ መጥተው 6ሺ ያህል ሰዎች በእጃቸው መንኩሰዋል::
+ምናኔን በማስፋፋታቸውና ሥርዓቱን በማስተማራቸውም "አቡሆሙ ለመነኮሳት ዘኢትዮዽያ-የኢትዮዽያ መነኮሳት አባት" ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ በሕይወታቸው ከተጋድሎ ባሻገር በወንጌል አገልግሎትና መጻሕፍትን በማዘጋጀትም ደክመዋል::
+ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀልም ወዳጆቻቸው ነበሩ:: በተራራው ግርጌ ያለችውን ኪዳነ ምሐረትን ለሴቶች ሲገድሟት ቀዳሚዋ መነኮስ እናታቸው ንግስት እድና ሁናለች::
+ጻድቁ ንጹሕ ሕይወታቸውን ፈጽመው በተወለዱ በ99 ዓመታቸው በዚህ ቀን በገዳሙ በስተምሥራቅ አካባቢ ተሰውረው ብሔረ ሕያዋን ገብተዋል:: ጌታም 15 ትውልድን የሚያስምር የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል::
+" ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ "+
✞✞✞ በዘመነ ሐዋርያት በዚህ ስም የሚጠሩ አባቶች 2 ነበሩ:: አንደኛው ከ12ቱ ሐዋርያት ሲቆጠር ዛሬ የምናከብረው ደግሞ ከ72ቱ አርድእት ይቆጠራል:: ቅዱስ ፊልዾስ ያደገው የኖረውም በቂሣርያ አካባቢ ሲሆን ባለ ትዳር የልጆች አባት ነው::
+ጌታ ሲጠራው እንኩዋ 4 ደናግል ሴቶች ልጆች ነበሩት:: ከጌታ ሕማማት በፊት ተልኮ አስተምሯል:: ከበዓለ ሃምሳ በኋላም 7ቱ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: (ሐዋ. 6) በቅዱስ እስጢፋኖስ መሪነትም 8ሺውን ማሕበር አገልግሏል::
+ቅዱስ እስጢፋኖስ ተገድሎ 8ሺው ማሕበር ሲበተንም ቅዱስ ፊልዾስ 4ቱን ልጆቹን አስከትሎ ወደ ሰማርያ ወርዷል:: በዚያም መሠሪ ስምዖንን ጨምሮ የሃገሪቱን ሰዎች አሳምኖ አጥምቁዋል::
+መቼም ቢሆን እኛ ኢትዮዽያውያን የማንዘነጋው ግን ጃንደረባውን ባኮስን ማጥመቁን እና ለሃገራችን የወንጌልን ብርሃን መላኩን ነው:: ጃንደረባው ቅዱስ ባኮስ ከጉዞ መልስ ትንቢተ ኢሳይያስን (ኢሳ. 53) ሲያነብ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ቀርቦ ምሥጢረ ሥጋዌን አስረድቶታል::
+ሠረገላውም ቁሞለት ቅዱስ ባኮስን አጥምቆት ተነጥቆ ሔዷል:: (ሐዋ. 8:26) ቅዱስ ፊልዾስ በቀሪ ዘመኑ ከተባረኩ 4 ደናግል ልጆቹ ጋር ሲሰብክ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል::
+" ሙሽራው ቅዱስ ሙሴ "+
✞✞✞ የዚህ ቅዱስ ወጣት ታሪክ ደስ የሚልም: የሚገርምም ነው:: በሮም ከተማ በምጽዋት: በጾምና በጸሎት ከተቃኙ ሃብታሞች (መስፍንያኖስና አግልያስ) ተወልዶ: በሥርዓቱ አድጐ: መጻሕፍትን ተምሮ በተክሊል አጋቡት::
+በሠርጉ ማግስት ሙሽሪትን ቢያያት በጣም ታምራለች:: "ይህ ሁሉ ውበትና ምቾት ከንቱ አይደለምን!" ብሎ በሌሊት ጠፍቶ: ነዳያንን መስሎ ከሮም ሃገረ ሮሆ (ሶርያ አካባቢ) ሔደ::
+በዚያም በፍጹም ምናኔ: በ7 ቀን አንዲት ማዕድ እየበላ: በረንዳ ላይ እየተኛና እየለመነ ለዓመታት ኖረ:: ሁሌም ቀን የለመነውን ማታ ለነዳያን አካፍሎ እርሱ ሲጸልይ ያድር ነበር:: በአካባቢው ክብሩ ሲገለጽበትም የሐዋርያውን የቅዱስ ዻውሎስን በረከት ፍለጋ ወደ ጠርሴስ ሔደ::
+ነገር ግን ጥቅል ነፋስ መርከቧን ገፍቶ ሮም አደረሳት:: ቅዱስ ሙሴም "የአምላክ ፈቃድ ነው" ብሎ በወላጆቹ ደጅ ተኝቶ ለ12 ዓመታት ተጋደለ:: ወላጆቹ ፈልገው ስላጡት በበራቸው የወደቀው ነዳይ እርሱ ይሆናል ብለው አልጠረጠሩም::
+ከብዙ ተጋድሎም በኋላም ዜና ሕይወቱን ጽፎ በዚህች ቀን: በዕለተ እሑድ ዐርፏል:: ጌታችንም "መታሰቢያህን ያደረገውን ሁሉ ካልተጠራጠረ እምረዋለሁ" ብሎታል::
በዚያም ሕዝቡ: ካህናቱና ሊቀ ዻዻሳቱን ጌታ አዟቸው አግኝተውታል:: ወላጆቹ ማንነቱን በለዩ ጊዜም ታላቅ ለቅሶን አልቅሰዋል:: ሥጋውም ብዙ ተአምራትን አድርጉዋል::
+" ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ "+
✞✞✞ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ በሃገራቸው ልሳን 'አብደል መሲሕ' ይባላል:: ለቅዱስ ሙሴና ለሌሎችም ሙሽርነትን ትቶ መመነንን ያስተማረ እርሱ ነው:: አባቱ ታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሲሆን እናቱ መርኬዛ ትባላለች:: የጻድቃን ትውልድ የተባረከ ነውና (መዝ. 111:1) ታላቁ አቡነ ኪሮስ አጐቱ ናቸው::
+ስለዚህ ቅዱስ ምን እነግራቹሃለሁ! ሙሉ ታሪኩ ከቅዱስ ሙሴ ጋር ተመሳሳይ ነውና:: ልዩነቱ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ በገዛ ፍቃዱ አካሉ በመቁሰሉ ምክንያት ሰዎች ሊለዩት አልቻሉም ነበር::
+በአርማንያ: በእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን ደጅ ለ15 ዓመታት ሲጋደል ወደ ወላጆቹ ሃገር ቁስጥንጥንያ ተመልሶ ለ15 ዓመታት ተፈትኗል:: ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆንም የአባቱ ባሮች በጥፊ ይመቱት: ጽሕሙን (ጺሙን) ይነጩት: ቆሻሻ ይደፉበት: ሽንታቸውንም ይሸኑበት ነበር::
+ለእርሱ ወዳጆቹ ውሾች ነበሩ:: በአባቱ ደጅ ለ15 ዓመታት መከራን ከተቀበለ በኋላ "ጌታ ሆይ! የአባቴ አገልጋዮች በእኔ ላይ ያደረጉትን ሁሉ በደል አድርገለህ አትቁጠርባቸው" አለ:: በዚህች ቀን ሲያርፍም ጌታችን 7ቱን ሊቃነ መላእክት ከነ ሠራዊታቸው አስከትሎ ወርዶ በክብር አሳርጐታል:: አጠቃላይ የገድል ዓመታቱም 30 ናቸው::
✞✞✞ አምላከ ቅዱሳን ለእነርሱ ካደለው ፍቅራቸው ለእኛም አይንሳን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::
+ጥቅምት 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አቡነ ዘሚካኤል (አረጋዊ)
2.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
4.ቅዱስ ሙሴ መርዓዊ
5.ቅድስት እድና (የአረጋዊ እናት)
6.አባ ማትያስ (የአረጋዊ ረድዕ)
✞✞✞ ጥቅምት 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞
✞✞✞ አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ ✞✞✞
✞✞✞ በሃገራችን ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ እኒህ ጻድቅ ናቸው:: ጻድቁ የተወለዱት በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን አጋማሽ ኣካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅና ቅድስት እድና ይባላሉ:: የተለወለዱበት አካባቢም ሮም ነው::
+ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው:: ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረ አምላክ ተብለዋል:: በኢትዮዽያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ::
+በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል:: ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር 7 ያህል የቤተ መንግስት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል::
+"የት ልሒድ" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮዽያን አሳያቸው:: ተመልሰውም ለ8 ባልንጀሮቻቸው "ሃገርስ ባሳየሁዋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር" ብለው ከ8ቱ ጋር ወደ ኢትዮዽያ መጡ::
+በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ:: ወደ ሃገራችን የመጡ በ470ዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል:: በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጻሕፍትን እየተረጐሙ: ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል::
+ለሥራ በተለያዩ ጊዜም አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ብዙ ደክመዋል:: በመጨረሻ ግን ደብረ ዳሞን (ደብረ ሃሌ ሉያን) አይተው ወደዷት:: የሚወጡበት ቢያጡም ጅራቱ 60 ክንድ የሚያህል ዘንዶ ተሸክሞ ከላይ አድርሷቸዋል::
+እንደ ወጡም "ሃሌ ሉያ ለአብ: ሃሌ ሉያ ለወልድ: ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ" ብለው ቢያመሰግኑ ከሰማይ ሕብስት ወርዶላቸው ተመግበዋል:: በዚህም ቦታዋ "ደብረ ሃሌ ሉያ" ተብላለች:: ጻድቁ ቦታውን ከገደሙ በኋላ ከተለያየ ቦታ መጥተው 6ሺ ያህል ሰዎች በእጃቸው መንኩሰዋል::
+ምናኔን በማስፋፋታቸውና ሥርዓቱን በማስተማራቸውም "አቡሆሙ ለመነኮሳት ዘኢትዮዽያ-የኢትዮዽያ መነኮሳት አባት" ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ በሕይወታቸው ከተጋድሎ ባሻገር በወንጌል አገልግሎትና መጻሕፍትን በማዘጋጀትም ደክመዋል::
+ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀልም ወዳጆቻቸው ነበሩ:: በተራራው ግርጌ ያለችውን ኪዳነ ምሐረትን ለሴቶች ሲገድሟት ቀዳሚዋ መነኮስ እናታቸው ንግስት እድና ሁናለች::
+ጻድቁ ንጹሕ ሕይወታቸውን ፈጽመው በተወለዱ በ99 ዓመታቸው በዚህ ቀን በገዳሙ በስተምሥራቅ አካባቢ ተሰውረው ብሔረ ሕያዋን ገብተዋል:: ጌታም 15 ትውልድን የሚያስምር የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል::
+" ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ "+
✞✞✞ በዘመነ ሐዋርያት በዚህ ስም የሚጠሩ አባቶች 2 ነበሩ:: አንደኛው ከ12ቱ ሐዋርያት ሲቆጠር ዛሬ የምናከብረው ደግሞ ከ72ቱ አርድእት ይቆጠራል:: ቅዱስ ፊልዾስ ያደገው የኖረውም በቂሣርያ አካባቢ ሲሆን ባለ ትዳር የልጆች አባት ነው::
+ጌታ ሲጠራው እንኩዋ 4 ደናግል ሴቶች ልጆች ነበሩት:: ከጌታ ሕማማት በፊት ተልኮ አስተምሯል:: ከበዓለ ሃምሳ በኋላም 7ቱ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: (ሐዋ. 6) በቅዱስ እስጢፋኖስ መሪነትም 8ሺውን ማሕበር አገልግሏል::
+ቅዱስ እስጢፋኖስ ተገድሎ 8ሺው ማሕበር ሲበተንም ቅዱስ ፊልዾስ 4ቱን ልጆቹን አስከትሎ ወደ ሰማርያ ወርዷል:: በዚያም መሠሪ ስምዖንን ጨምሮ የሃገሪቱን ሰዎች አሳምኖ አጥምቁዋል::
+መቼም ቢሆን እኛ ኢትዮዽያውያን የማንዘነጋው ግን ጃንደረባውን ባኮስን ማጥመቁን እና ለሃገራችን የወንጌልን ብርሃን መላኩን ነው:: ጃንደረባው ቅዱስ ባኮስ ከጉዞ መልስ ትንቢተ ኢሳይያስን (ኢሳ. 53) ሲያነብ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ቀርቦ ምሥጢረ ሥጋዌን አስረድቶታል::
+ሠረገላውም ቁሞለት ቅዱስ ባኮስን አጥምቆት ተነጥቆ ሔዷል:: (ሐዋ. 8:26) ቅዱስ ፊልዾስ በቀሪ ዘመኑ ከተባረኩ 4 ደናግል ልጆቹ ጋር ሲሰብክ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል::
+" ሙሽራው ቅዱስ ሙሴ "+
✞✞✞ የዚህ ቅዱስ ወጣት ታሪክ ደስ የሚልም: የሚገርምም ነው:: በሮም ከተማ በምጽዋት: በጾምና በጸሎት ከተቃኙ ሃብታሞች (መስፍንያኖስና አግልያስ) ተወልዶ: በሥርዓቱ አድጐ: መጻሕፍትን ተምሮ በተክሊል አጋቡት::
+በሠርጉ ማግስት ሙሽሪትን ቢያያት በጣም ታምራለች:: "ይህ ሁሉ ውበትና ምቾት ከንቱ አይደለምን!" ብሎ በሌሊት ጠፍቶ: ነዳያንን መስሎ ከሮም ሃገረ ሮሆ (ሶርያ አካባቢ) ሔደ::
+በዚያም በፍጹም ምናኔ: በ7 ቀን አንዲት ማዕድ እየበላ: በረንዳ ላይ እየተኛና እየለመነ ለዓመታት ኖረ:: ሁሌም ቀን የለመነውን ማታ ለነዳያን አካፍሎ እርሱ ሲጸልይ ያድር ነበር:: በአካባቢው ክብሩ ሲገለጽበትም የሐዋርያውን የቅዱስ ዻውሎስን በረከት ፍለጋ ወደ ጠርሴስ ሔደ::
+ነገር ግን ጥቅል ነፋስ መርከቧን ገፍቶ ሮም አደረሳት:: ቅዱስ ሙሴም "የአምላክ ፈቃድ ነው" ብሎ በወላጆቹ ደጅ ተኝቶ ለ12 ዓመታት ተጋደለ:: ወላጆቹ ፈልገው ስላጡት በበራቸው የወደቀው ነዳይ እርሱ ይሆናል ብለው አልጠረጠሩም::
+ከብዙ ተጋድሎም በኋላም ዜና ሕይወቱን ጽፎ በዚህች ቀን: በዕለተ እሑድ ዐርፏል:: ጌታችንም "መታሰቢያህን ያደረገውን ሁሉ ካልተጠራጠረ እምረዋለሁ" ብሎታል::
በዚያም ሕዝቡ: ካህናቱና ሊቀ ዻዻሳቱን ጌታ አዟቸው አግኝተውታል:: ወላጆቹ ማንነቱን በለዩ ጊዜም ታላቅ ለቅሶን አልቅሰዋል:: ሥጋውም ብዙ ተአምራትን አድርጉዋል::
+" ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ "+
✞✞✞ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ በሃገራቸው ልሳን 'አብደል መሲሕ' ይባላል:: ለቅዱስ ሙሴና ለሌሎችም ሙሽርነትን ትቶ መመነንን ያስተማረ እርሱ ነው:: አባቱ ታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሲሆን እናቱ መርኬዛ ትባላለች:: የጻድቃን ትውልድ የተባረከ ነውና (መዝ. 111:1) ታላቁ አቡነ ኪሮስ አጐቱ ናቸው::
+ስለዚህ ቅዱስ ምን እነግራቹሃለሁ! ሙሉ ታሪኩ ከቅዱስ ሙሴ ጋር ተመሳሳይ ነውና:: ልዩነቱ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ በገዛ ፍቃዱ አካሉ በመቁሰሉ ምክንያት ሰዎች ሊለዩት አልቻሉም ነበር::
+በአርማንያ: በእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን ደጅ ለ15 ዓመታት ሲጋደል ወደ ወላጆቹ ሃገር ቁስጥንጥንያ ተመልሶ ለ15 ዓመታት ተፈትኗል:: ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆንም የአባቱ ባሮች በጥፊ ይመቱት: ጽሕሙን (ጺሙን) ይነጩት: ቆሻሻ ይደፉበት: ሽንታቸውንም ይሸኑበት ነበር::
+ለእርሱ ወዳጆቹ ውሾች ነበሩ:: በአባቱ ደጅ ለ15 ዓመታት መከራን ከተቀበለ በኋላ "ጌታ ሆይ! የአባቴ አገልጋዮች በእኔ ላይ ያደረጉትን ሁሉ በደል አድርገለህ አትቁጠርባቸው" አለ:: በዚህች ቀን ሲያርፍም ጌታችን 7ቱን ሊቃነ መላእክት ከነ ሠራዊታቸው አስከትሎ ወርዶ በክብር አሳርጐታል:: አጠቃላይ የገድል ዓመታቱም 30 ናቸው::
✞✞✞ አምላከ ቅዱሳን ለእነርሱ ካደለው ፍቅራቸው ለእኛም አይንሳን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::
+ጥቅምት 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አቡነ ዘሚካኤል (አረጋዊ)
2.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
4.ቅዱስ ሙሴ መርዓዊ
5.ቅድስት እድና (የአረጋዊ እናት)
6.አባ ማትያስ (የአረጋዊ ረድዕ)
❤1
++"+ ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል:: ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል:: ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ውሃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላቹሃለሁ ዋጋው አይጠፋበትም:: +"+ (ማቴ. 10:41)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
ጥቅምት 9 2018 ዓ.ም
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
ጥቅምት 9 2018 ዓ.ም
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
❤3
"ዘእምደብረ ደናግል አባ ኤልያስ
ወትሩፈ ምግባር አረጋዊ
ዘውገ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ
አማን ዘቀደሶ መንፈስ ቅዱስ"
ዚቅ ዘቅዱስ ያሬድ
እንኳን ለቅዱሳን አባቶቻችን አቡነ አረጋዊ እና ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
ጥቅምት 13 2018 ዓ.ም
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
ወትሩፈ ምግባር አረጋዊ
ዘውገ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ
አማን ዘቀደሶ መንፈስ ቅዱስ"
ዚቅ ዘቅዱስ ያሬድ
እንኳን ለቅዱሳን አባቶቻችን አቡነ አረጋዊ እና ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
ጥቅምት 13 2018 ዓ.ም
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
❤6
ሥርዓተ ማኅሌት ዘጥቅምት አቡነ አረጋዊ
🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶
ጥቅምት 14 2018 ዓ.ም
🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶
ጥቅምት 14 2018 ዓ.ም
🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔸🔶
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://www.group-telegram.com/weludebirhane.com
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ
😇2❤1🙏1
