Telegram Group & Telegram Channel
" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል" - የዕድሜ ባለፀጋዉ አቶ ማኖ ማገሶ

➡️ " ከአምስተኛ ክፍል የወረዳ አልፎም የአዉራጃ አስተዳዳሪ ሆኜ ነበር ፤ ትክክለኛዉ ዕድሜዬ 91 ነዉ ! "

አቶ ማኖ ማገሶ የ85 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ሲሆኑ ዘንድሮ በሁለተኛዉ ዙር የፈተና ፕሮግራም ከካቻ ካሻሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ካቀኑ የ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ዉስጥ አንዱ ናቸዉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም በልጃቸዉ በኩል አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።

ከልጅ ልጃቸዉ ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልፀዉ " ትምህርት በዕድሜ ሊገደብ አይገባም " ሲሉ ሃሳባቸው አጋርተዋል።

የ5 ወንዶችና የ6ሴቶች የ11 ልጆች አባት እንደሆኑ የገለፁት አቶ ማኖ በንጉሱ ዘመን በሁለት ዓመት ዉስጥ በነበራቸዉ ቀልጣፋ የትምህርት አቀባበል ክፍል እያጠፉ 5ኛ ክፍል መድረሳቸዉንና ከ5ኛ ክፍል ተወስደዉ የቦንኬ ወረዳ አመራር ተደርገዉ ተሹመዉ እንደነበርና ባሳዩት ጠንካራ አመራርም የቀድሞው የጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር በጋርዱላ አውራጃ የገበሬ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ይሰሩ እንደነበር አስታዉሰዋል።

በኋላም ደርግ መንበረ ስልጣኑን ሲይዝ ለእስር ተዳርገዉ ለ21 ዓመታት በአርባምንጭ ማረሚያ ታስረዉ መቆየታቸዉንና ደርግ ከወደቀ በኋላ ከማረሚያ ወጥተዉ ልጆቻቸዉን በማስተማር ቦታ ቦታ ካስያዙ በኋላ አቋርጠዉ የቆዩትን ትምህርት በመቀጠል ዘንድሮ በትምህርት መረጃ ላይ 85 ዓመት እሳቸዉ " ትክክለኛ ዕድሜዬ ነዉ " በሚሉት 91 ዓመታቸዉ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ከልጅ ልጃቸዉ ጋር አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልጸዋል።

ለትምህርት ካላቸዉ ጥልቅ ፍቅር የተነሳ በአመራርነት ዘመናቸዉ በርካታ ትምህርት ቤቶችን እንዳስገነቡ የገለፁት አቶ ማኖ እሳቸዉ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት አግብተዉ ትምህርታቸዉን አቋርጠዉ የነበሩ ልጆቻቸዉን ጭምር ከተፈቱ በኋላ ከባሎቻቸዉ ጭምር እንዲማሩ አድርገዉ በአሁኑ ሰዓት በመንግስት ስራ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፤ ጥሩ ዉጤት አምጥቼ ዩኒቨርሲቲ እገባለሁ " ብለዋል።

" ትምህርት በእድሜ የማይገደብ የሕይወት ምግብ ነዉ " ሲሉ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአቶ ማኖ ማገሶን ፅናታቸውን እያደነቀ መልካም ፈተና እንዲሆንላቸው ይመኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
👏1.4K1.08K🤔69🙏39😭38🥰22😱19😡18🕊17💔13😢6



group-telegram.com/tikvahethiopia/98230
Create:
Last Update:

" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል" - የዕድሜ ባለፀጋዉ አቶ ማኖ ማገሶ

➡️ " ከአምስተኛ ክፍል የወረዳ አልፎም የአዉራጃ አስተዳዳሪ ሆኜ ነበር ፤ ትክክለኛዉ ዕድሜዬ 91 ነዉ ! "

አቶ ማኖ ማገሶ የ85 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ሲሆኑ ዘንድሮ በሁለተኛዉ ዙር የፈተና ፕሮግራም ከካቻ ካሻሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ካቀኑ የ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ዉስጥ አንዱ ናቸዉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም በልጃቸዉ በኩል አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።

ከልጅ ልጃቸዉ ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልፀዉ " ትምህርት በዕድሜ ሊገደብ አይገባም " ሲሉ ሃሳባቸው አጋርተዋል።

የ5 ወንዶችና የ6ሴቶች የ11 ልጆች አባት እንደሆኑ የገለፁት አቶ ማኖ በንጉሱ ዘመን በሁለት ዓመት ዉስጥ በነበራቸዉ ቀልጣፋ የትምህርት አቀባበል ክፍል እያጠፉ 5ኛ ክፍል መድረሳቸዉንና ከ5ኛ ክፍል ተወስደዉ የቦንኬ ወረዳ አመራር ተደርገዉ ተሹመዉ እንደነበርና ባሳዩት ጠንካራ አመራርም የቀድሞው የጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር በጋርዱላ አውራጃ የገበሬ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ይሰሩ እንደነበር አስታዉሰዋል።

በኋላም ደርግ መንበረ ስልጣኑን ሲይዝ ለእስር ተዳርገዉ ለ21 ዓመታት በአርባምንጭ ማረሚያ ታስረዉ መቆየታቸዉንና ደርግ ከወደቀ በኋላ ከማረሚያ ወጥተዉ ልጆቻቸዉን በማስተማር ቦታ ቦታ ካስያዙ በኋላ አቋርጠዉ የቆዩትን ትምህርት በመቀጠል ዘንድሮ በትምህርት መረጃ ላይ 85 ዓመት እሳቸዉ " ትክክለኛ ዕድሜዬ ነዉ " በሚሉት 91 ዓመታቸዉ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ከልጅ ልጃቸዉ ጋር አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልጸዋል።

ለትምህርት ካላቸዉ ጥልቅ ፍቅር የተነሳ በአመራርነት ዘመናቸዉ በርካታ ትምህርት ቤቶችን እንዳስገነቡ የገለፁት አቶ ማኖ እሳቸዉ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት አግብተዉ ትምህርታቸዉን አቋርጠዉ የነበሩ ልጆቻቸዉን ጭምር ከተፈቱ በኋላ ከባሎቻቸዉ ጭምር እንዲማሩ አድርገዉ በአሁኑ ሰዓት በመንግስት ስራ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፤ ጥሩ ዉጤት አምጥቼ ዩኒቨርሲቲ እገባለሁ " ብለዋል።

" ትምህርት በእድሜ የማይገደብ የሕይወት ምግብ ነዉ " ሲሉ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአቶ ማኖ ማገሶን ፅናታቸውን እያደነቀ መልካም ፈተና እንዲሆንላቸው ይመኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/98230

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more. False news often spreads via public groups, or chats, with potentially fatal effects. Some people used the platform to organize ahead of the storming of the U.S. Capitol in January 2021, and last month Senator Mark Warner sent a letter to Durov urging him to curb Russian information operations on Telegram. Despite Telegram's origins, its approach to users' security has privacy advocates worried. Stocks dropped on Friday afternoon, as gains made earlier in the day on hopes for diplomatic progress between Russia and Ukraine turned to losses. Technology stocks were hit particularly hard by higher bond yields.
from ar


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American