Telegram Group & Telegram Channel
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም

"...ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ እንጂ ሁል ጊዜ በጥፋት መንገድ አትመላለሱ፤ ሞት ሳታስቡት በድንገት ይመጣባችኋልና፡፡ የሥጋ ምቾትም ንስሓን አይፈልግምና ለጥፋት ይዳርጋል፡፡

የመጨረሻው ቀን መጥቶ ሳያገኘን በንስሓ መንገድ እንመላለስ፡፡ የማይቀረው ሞት ሲመጣ ሁለተኛው ሞት እንዳያገኘን በቅድስና ሆነን እንጠብቅ፡፡ በሃይማኖት መጽናትም የድካማችንን ፍሬ እናግኝ። በዚህች ዓለም መልካሙን ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን ጋር የክብር አክሊል እንቀዳጅ ዘንድ፡፡ ሰው ታይቶ የሚጠፋውን የዚህን ዓለም አክሊል ለመቀዳጀት በወታደር እና በሠረገላ ጦርነት ይከፍታሉ፤ ጊዜአዊ የሆነ የዚህን ዓለም ደስታና ሐዘን ለመቅመስ ነው፡፡

እንግዲህ የዚህን ዓለም ዘውድ ለመቀዳጀት ሩጫው ይህን ያህል ከሆነ ዘላለማዊውን ክብር፣ ሰማያዊውን አክሊል ለመቀዳጀት ውድድሩ ምንኛ ታላቅ ይሆን? ስለዚህ ሐዋርያው ‹‹የሚታገል ሁሉ በሁሉ ነገር ይታገሣል፤ እነርሱስ የሚጠፋውንና የሚያልፈውን አክሊል ያገኙ ዘንድ ይበረታሉ፤ እኛ ግን የማያልፈውን አክሊል ለማግኘት እንታገሣለን›› (1ቆሮ. 9፥25-26) አለን፡፡

እንግዲህ እርጉም በሆነው ጠላታችን ላይ ድል እስክናገኝ ድረስ ከተንኮል ሥራውም እስክናመልጥ ድረስ የተጋድሎአችንን መሣርያ ንጽሕና ማድረግ ይገባናል፡፡ ክፉ የሆነው ጠላታችን እኛ ትኁታን ስንሆን ይቀናብናልና ይዋጋናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ከጠላት ቀስት የምንድንበት የበለሳን መድኃኒት ሰጠን፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር ያስተማረን የንስሓ መድኃኒት ነው፡፡

በእውነት ለቀረበ፣ ከልቡም ተጸጽቶ ለተመለሰ ይህ መድኃኒት ፍጹም የሚያድን ነው፡፡ ነገር ግን መድኃኒቱ የተሰረቀ በደል ያለበትን ገንዘብ በእጃቸው ይዘው፣ የረከሰ ሰውነታቸውን እየወደዱ በአፋቸው ብቻ ‹‹አድነን›› ለሚሉት አይደለም፡፡

ዳግመኛ በቀደመ ርኵሰታቸው የሚወቀሱትን የወቀሳ ድምፅ ስሙ፡፡ እንደዚሁም በመተላለፋቸው እራሳቸውን እየወቀሱ ዳግመኛ ወደ ጥፋት እንዳይመለሱ የሚጠነቀቁትን ስሙ፤ በግብርም እነርሱን ምሰሉ፡፡ ሕሊናን ሁሉ ወደሚመረምረው ወደ እርሱ ሁለት ልብ ሆናችሁ አትቅረቡ፡፡ የተሰወረውን ሁሉ ያውቃልና በሁለት መንገድ አትመላለሱ፡፡

እንግዲህ ንስሓ ለመግባት ፍጠኑ እንጂ ወደ አረንቋ አትመለሱ፡፡ በቸርነቱ ፍቅር ታጥባችሁ ንጹሐን ሁኑ እንጂ ዕዳችሁ ከተሰረዘላችሁ በኋላ ገንዘቡ እንደ ወደመበት ሰው ዳግመኛ ወደ ዕዳ አትግቡ፡፡

ከምርኮ የተለቀቀ ሰው በምንም መልኩ ዳግመኛ መማረክ፣ ወደ ምርኮው ቦታ ተመልሶ መሔድ አይፈልግም፡፡ ወይም ከግዞት ሥቃይ ከወጣ በኋላ ዳግመኛ መገዛት አይፈልግም፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደ ግዞት እንዳይገባ ይጸልያል፡፡ እንግዲህ እናንተም ከገዳይ ቀንበር ከወጣችሁ በኋላ ዳግመኛ እንዳትገዙ ጸልዩ፤ በጥልፍልፉ ወጥመድም እንዳትያዙ ትጉ፡፡"

(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
85🙏28🕊2



group-telegram.com/beteafework/5727
Create:
Last Update:

በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም

"...ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ እንጂ ሁል ጊዜ በጥፋት መንገድ አትመላለሱ፤ ሞት ሳታስቡት በድንገት ይመጣባችኋልና፡፡ የሥጋ ምቾትም ንስሓን አይፈልግምና ለጥፋት ይዳርጋል፡፡

የመጨረሻው ቀን መጥቶ ሳያገኘን በንስሓ መንገድ እንመላለስ፡፡ የማይቀረው ሞት ሲመጣ ሁለተኛው ሞት እንዳያገኘን በቅድስና ሆነን እንጠብቅ፡፡ በሃይማኖት መጽናትም የድካማችንን ፍሬ እናግኝ። በዚህች ዓለም መልካሙን ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን ጋር የክብር አክሊል እንቀዳጅ ዘንድ፡፡ ሰው ታይቶ የሚጠፋውን የዚህን ዓለም አክሊል ለመቀዳጀት በወታደር እና በሠረገላ ጦርነት ይከፍታሉ፤ ጊዜአዊ የሆነ የዚህን ዓለም ደስታና ሐዘን ለመቅመስ ነው፡፡

እንግዲህ የዚህን ዓለም ዘውድ ለመቀዳጀት ሩጫው ይህን ያህል ከሆነ ዘላለማዊውን ክብር፣ ሰማያዊውን አክሊል ለመቀዳጀት ውድድሩ ምንኛ ታላቅ ይሆን? ስለዚህ ሐዋርያው ‹‹የሚታገል ሁሉ በሁሉ ነገር ይታገሣል፤ እነርሱስ የሚጠፋውንና የሚያልፈውን አክሊል ያገኙ ዘንድ ይበረታሉ፤ እኛ ግን የማያልፈውን አክሊል ለማግኘት እንታገሣለን›› (1ቆሮ. 9፥25-26) አለን፡፡

እንግዲህ እርጉም በሆነው ጠላታችን ላይ ድል እስክናገኝ ድረስ ከተንኮል ሥራውም እስክናመልጥ ድረስ የተጋድሎአችንን መሣርያ ንጽሕና ማድረግ ይገባናል፡፡ ክፉ የሆነው ጠላታችን እኛ ትኁታን ስንሆን ይቀናብናልና ይዋጋናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ከጠላት ቀስት የምንድንበት የበለሳን መድኃኒት ሰጠን፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር ያስተማረን የንስሓ መድኃኒት ነው፡፡

በእውነት ለቀረበ፣ ከልቡም ተጸጽቶ ለተመለሰ ይህ መድኃኒት ፍጹም የሚያድን ነው፡፡ ነገር ግን መድኃኒቱ የተሰረቀ በደል ያለበትን ገንዘብ በእጃቸው ይዘው፣ የረከሰ ሰውነታቸውን እየወደዱ በአፋቸው ብቻ ‹‹አድነን›› ለሚሉት አይደለም፡፡

ዳግመኛ በቀደመ ርኵሰታቸው የሚወቀሱትን የወቀሳ ድምፅ ስሙ፡፡ እንደዚሁም በመተላለፋቸው እራሳቸውን እየወቀሱ ዳግመኛ ወደ ጥፋት እንዳይመለሱ የሚጠነቀቁትን ስሙ፤ በግብርም እነርሱን ምሰሉ፡፡ ሕሊናን ሁሉ ወደሚመረምረው ወደ እርሱ ሁለት ልብ ሆናችሁ አትቅረቡ፡፡ የተሰወረውን ሁሉ ያውቃልና በሁለት መንገድ አትመላለሱ፡፡

እንግዲህ ንስሓ ለመግባት ፍጠኑ እንጂ ወደ አረንቋ አትመለሱ፡፡ በቸርነቱ ፍቅር ታጥባችሁ ንጹሐን ሁኑ እንጂ ዕዳችሁ ከተሰረዘላችሁ በኋላ ገንዘቡ እንደ ወደመበት ሰው ዳግመኛ ወደ ዕዳ አትግቡ፡፡

ከምርኮ የተለቀቀ ሰው በምንም መልኩ ዳግመኛ መማረክ፣ ወደ ምርኮው ቦታ ተመልሶ መሔድ አይፈልግም፡፡ ወይም ከግዞት ሥቃይ ከወጣ በኋላ ዳግመኛ መገዛት አይፈልግም፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደ ግዞት እንዳይገባ ይጸልያል፡፡ እንግዲህ እናንተም ከገዳይ ቀንበር ከወጣችሁ በኋላ ዳግመኛ እንዳትገዙ ጸልዩ፤ በጥልፍልፉ ወጥመድም እንዳትያዙ ትጉ፡፡"

(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)

BY ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/beteafework/5727

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Multiple pro-Kremlin media figures circulated the post's false claims, including prominent Russian journalist Vladimir Soloviev and the state-controlled Russian outlet RT, according to the DFR Lab's report. Telegram has gained a reputation as the “secure” communications app in the post-Soviet states, but whenever you make choices about your digital security, it’s important to start by asking yourself, “What exactly am I securing? And who am I securing it from?” These questions should inform your decisions about whether you are using the right tool or platform for your digital security needs. Telegram is certainly not the most secure messaging app on the market right now. Its security model requires users to place a great deal of trust in Telegram’s ability to protect user data. For some users, this may be good enough for now. For others, it may be wiser to move to a different platform for certain kinds of high-risk communications. "The argument from Telegram is, 'You should trust us because we tell you that we're trustworthy,'" Maréchal said. "It's really in the eye of the beholder whether that's something you want to buy into." He adds: "Telegram has become my primary news source." As the war in Ukraine rages, the messaging app Telegram has emerged as the go-to place for unfiltered live war updates for both Ukrainian refugees and increasingly isolated Russians alike.
from us


Telegram ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
FROM American