Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሂጃብሂጃብ #አክሱም " ተከሳሾች የሰጡት አስተዳደራዊ ትእዛዝ መዝገቡ እልባት እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ #እንዳይተገበር ለጊዜው በእግድ እንዲቆይ ታዟል " - ፍርድ ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ክልከላ አድርገዋል በተባሉት አካላት ላይ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ህጋዊ ክስ…
#Update

🧕" የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ በመጣስ አሁንም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች / ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ ከልክሏል "  - የተማሪዎች ቤተሰቦች

👉 " የተጣሰ የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ የለም ፤ የትምህርት ህግ እና ደንብ ያከበሩ ተማሪዎች ወደ ክፍል ገብተው መማር ጀምረዋል ፤ ቀሪዎቹ እንዲመለሱ ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ ነን " -  የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር

የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም በፃፈው የእግድ ትእዛዝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው እንዲማሩ ፤ በክልከላ የተሳተፉ አካላት ለጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ቢያዝም ተግባራዊ አልሆነም ብለዋል የተማሪዎች ቤተሰቦች።

የተማሪ ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ (መቐለ) በሰጡት አስተያየት ፤ " የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር በተያያዘ በአክሱም ከተማ ፍርድ  ቤት በኩል በ5 አካላት ላይ የእግድ ደብዳቤ ቢያፅፍም ተግባራዊ አልሆነም ተጥሷል " ብለዋል። 

የእግድ ትእዛዙን ከጣሱት አንዱ የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሆኑን የጠቀሱት የተማሪ ቤተሰቦች ፤ " ትምህርት ቤቱ የእግድ ትእዛዙን በመጣስ ጥር 7 እና 8/2017 ዓ.ም ተማሪዎቹ ክፍል ገብተው እንዳይማሩ በማድረግ ተደራራቢ ጥፋቶች እየፈፀመ ነው " ሲሉ ከሰዋል። 

አስተያየት ሰጪዎቹ  " ከህግ በላይ መሆን ልክ አይደለም የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና የሃይማኖት መብት ይከበር " ሲሉ ምሬታቸው ገልፀዋል። 

በተማሪዎች ቤተሰቦች በኩል ለቀረበው አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ምላሽ የሰጡት የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ርእሰ መምህር ስዩም ካሕሳይ ፥ " ትምህርት ቤታችን ' የፍርድ ቤት እግድ እና ትእዛዝ በመጣስ ተማሪዎቹ እንዳይማሩ ከልክሏል ' የሚባለው ስህተት ነው " ብለዋል።   

" ለተማሪ ሴት ልጆቻችን በቅርብ እና በሩቅ ሆኖው ' እንቆረቆራለን ' ከሚሉት በላይ እናስብላቸዋለን " ያሉት ርእሰ መምህሩ " አሁንም ጉዳዩ ከሚገባው በላይ ማጋነን እና ማቀጣጠል እንዲሁም ለፓለቲካዊ ፍጆታ ማዋል ለአገር እና ህዝብ አይጠቅምም " ሲሉ አብራርተዋል።  

" የትምህርት ቤታችን አስተዳደር የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና እግድ ሳይጠብቅ የተፈጠረው አለመግባባት እንዲፈታ ሌት ተቀን በመስራት ላይ እንገኛለን " ሲሉ ገልጸው " የፍርድ ቤቱ ቃል አክብረን የትምህርት ቤቱ መምሪያ እና ደንብ በመጠበቅ ጥቂት የማይባሉ ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው መልሰናል የተቀሩት ለመመለስ ደግሞ በማያቋርጥ ጥረት ላይ እንገኛለን " ብለዋል።

" ከ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ የቀሩት እንዲካተቱ ከሚመለከታቸው አካላት ተከታታይ ስራዎች እየሰራን " ሲሉ አክለዋል።   

ከሂጃብ መልበስ ጋር ተያይዞ ከ2017 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲቀሩ  የሆኑት 159 የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጉዳይ ክልላዊ እና አገራዊ አጀንዳ ከመሆን በዘለለ በህግ እንዲታይ ወደ ፍርድ አምርቷል።

ከሂጃብ አጠቃቀም ክልከላ ጋር በተያያዘ ተሳታፊ ናቸው በተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ 5 አካላት ለጥር 16/2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ፤ ጎን ለጎን ደግሞ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም አዟል።  

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ዛሬ ጥር 8/2017 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ በፃፈው ደብዳቤ ፤ የሂጃብ መልበስ ክልከላው እንዲያነሳ አሳውቋል።

በተያያዘ መረጃ ከሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ጋር ተያይዞ ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ መከልከሉ ለመቃወም የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለዓርብ ጥር 9/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ እንዲካሄድ የጠራው እና የተፈቀደ ሰላማዊ ሰልፍ የጥምቀት በዓል ዋዜማ በመሆኑ ምክንያት ወደ ጥር 13/2017 ዓ.ም ማዘዋወሩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ  ከምክር ቤቱ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
1😡1.05K310👏118😭79🕊43🥰29🤔28😢24😱16🙏10



group-telegram.com/tikvahethiopia/93781
Create:
Last Update:

#Update

🧕" የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ በመጣስ አሁንም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች / ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ ከልክሏል "  - የተማሪዎች ቤተሰቦች

👉 " የተጣሰ የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ የለም ፤ የትምህርት ህግ እና ደንብ ያከበሩ ተማሪዎች ወደ ክፍል ገብተው መማር ጀምረዋል ፤ ቀሪዎቹ እንዲመለሱ ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ ነን " -  የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር

የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም በፃፈው የእግድ ትእዛዝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው እንዲማሩ ፤ በክልከላ የተሳተፉ አካላት ለጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ቢያዝም ተግባራዊ አልሆነም ብለዋል የተማሪዎች ቤተሰቦች።

የተማሪ ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ (መቐለ) በሰጡት አስተያየት ፤ " የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር በተያያዘ በአክሱም ከተማ ፍርድ  ቤት በኩል በ5 አካላት ላይ የእግድ ደብዳቤ ቢያፅፍም ተግባራዊ አልሆነም ተጥሷል " ብለዋል። 

የእግድ ትእዛዙን ከጣሱት አንዱ የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሆኑን የጠቀሱት የተማሪ ቤተሰቦች ፤ " ትምህርት ቤቱ የእግድ ትእዛዙን በመጣስ ጥር 7 እና 8/2017 ዓ.ም ተማሪዎቹ ክፍል ገብተው እንዳይማሩ በማድረግ ተደራራቢ ጥፋቶች እየፈፀመ ነው " ሲሉ ከሰዋል። 

አስተያየት ሰጪዎቹ  " ከህግ በላይ መሆን ልክ አይደለም የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና የሃይማኖት መብት ይከበር " ሲሉ ምሬታቸው ገልፀዋል። 

በተማሪዎች ቤተሰቦች በኩል ለቀረበው አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ምላሽ የሰጡት የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ርእሰ መምህር ስዩም ካሕሳይ ፥ " ትምህርት ቤታችን ' የፍርድ ቤት እግድ እና ትእዛዝ በመጣስ ተማሪዎቹ እንዳይማሩ ከልክሏል ' የሚባለው ስህተት ነው " ብለዋል።   

" ለተማሪ ሴት ልጆቻችን በቅርብ እና በሩቅ ሆኖው ' እንቆረቆራለን ' ከሚሉት በላይ እናስብላቸዋለን " ያሉት ርእሰ መምህሩ " አሁንም ጉዳዩ ከሚገባው በላይ ማጋነን እና ማቀጣጠል እንዲሁም ለፓለቲካዊ ፍጆታ ማዋል ለአገር እና ህዝብ አይጠቅምም " ሲሉ አብራርተዋል።  

" የትምህርት ቤታችን አስተዳደር የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና እግድ ሳይጠብቅ የተፈጠረው አለመግባባት እንዲፈታ ሌት ተቀን በመስራት ላይ እንገኛለን " ሲሉ ገልጸው " የፍርድ ቤቱ ቃል አክብረን የትምህርት ቤቱ መምሪያ እና ደንብ በመጠበቅ ጥቂት የማይባሉ ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው መልሰናል የተቀሩት ለመመለስ ደግሞ በማያቋርጥ ጥረት ላይ እንገኛለን " ብለዋል።

" ከ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ የቀሩት እንዲካተቱ ከሚመለከታቸው አካላት ተከታታይ ስራዎች እየሰራን " ሲሉ አክለዋል።   

ከሂጃብ መልበስ ጋር ተያይዞ ከ2017 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲቀሩ  የሆኑት 159 የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጉዳይ ክልላዊ እና አገራዊ አጀንዳ ከመሆን በዘለለ በህግ እንዲታይ ወደ ፍርድ አምርቷል።

ከሂጃብ አጠቃቀም ክልከላ ጋር በተያያዘ ተሳታፊ ናቸው በተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ 5 አካላት ለጥር 16/2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ፤ ጎን ለጎን ደግሞ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም አዟል።  

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ዛሬ ጥር 8/2017 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ በፃፈው ደብዳቤ ፤ የሂጃብ መልበስ ክልከላው እንዲያነሳ አሳውቋል።

በተያያዘ መረጃ ከሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ጋር ተያይዞ ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ መከልከሉ ለመቃወም የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለዓርብ ጥር 9/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ እንዲካሄድ የጠራው እና የተፈቀደ ሰላማዊ ሰልፍ የጥምቀት በዓል ዋዜማ በመሆኑ ምክንያት ወደ ጥር 13/2017 ዓ.ም ማዘዋወሩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ  ከምክር ቤቱ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA







Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93781

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

You may recall that, back when Facebook started changing WhatsApp’s terms of service, a number of news outlets reported on, and even recommended, switching to Telegram. Pavel Durov even said that users should delete WhatsApp “unless you are cool with all of your photos and messages becoming public one day.” But Telegram can’t be described as a more-secure version of WhatsApp. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed. Telegram does offer end-to-end encrypted communications through Secret Chats, but this is not the default setting. Standard conversations use the MTProto method, enabling server-client encryption but with them stored on the server for ease-of-access. This makes using Telegram across multiple devices simple, but also means that the regular Telegram chats you’re having with folks are not as secure as you may believe. "This time we received the coordinates of enemy vehicles marked 'V' in Kyiv region," it added. Investors took profits on Friday while they could ahead of the weekend, explained Tom Essaye, founder of Sevens Report Research. Saturday and Sunday could easily bring unfortunate news on the war front—and traders would rather be able to sell any recent winnings at Friday’s earlier prices than wait for a potentially lower price at Monday’s open.
from ca


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American