Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" ' ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ ናቸው ' የሚለው አመራሩ የሚጠቀምበት ማጭበርበሪያ ነው " - አቶ ጌታቸው ረዳ " ህወሓት እና የትግራይ ህዝብ አንድ ናቸው " የሚለው አመራሩ የሚጠቀምበት ማጭበርበሪያ እንደሆነ የቀድሞ የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንትና የአሁኑ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ። ይህ የተናገሩት ከ ' ፋና ቴሌቪዥን ' ጋር በነበራቸው ዘልግ…
" እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ እስካሁን የታገስኩት ይበቃኛል " - አቶ ጌታቸው ረዳ

በትግራይ ያለው ህገወጥ የወርቅ ንግድ  ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ የጀመረ ሳይሆን በጦርነቱ ጊዜም ሳይቀር ሲሰራ የነበረ እንደሆነ የቀድሞው የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና የአሁኑ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አደረጉ።

አቶ ጌታቸው፤ "ብዙ ሰው የወርቅ ንግድ የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈራረምን በኃላ የጀመር ይመስለዋል" ያሉ ሲሆን ግን ጦርነቱም እየተካሄደ ንግዱ ነበር ብለዋል።

"እኔ የማምንበትን ትግል ነው ያካሄድኩት ብዬ አምናለሁ በዛ በማምንበት ትግል ውስጥ የትግራይን ህዝብ አጀንዳ ይዘው የታገሉ ብዙ የጦር መኮንኖች አሉ ለሰሩት ስራ ያለኝ ክብር በፍጹም አይቀንስም ግን ደግሞ ገና ገና ጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ይበላ በነበረበት ወቅት ሳይቀር ምሽግ ለመቆፈር ብለን የወሰድነው ኤክስካቫተር ወርቅ ለመልቀም ይጠቀሙበት የነበሩ አዛዦችም ነበሩ" ሲሉ አጋልጠዋል።

"ሲዋሹ በጣም ነው የሚገርመኝ" ያሉት አቶ ጌታቸው "እኔ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል እስካሁን የታገስኩትም ይበቃኛል" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው "የኤርትራን ሰራዊት እናፍርሰው" በሚል አላማ ዘመቻ የጀመረና ዘመቻውን የሚመራው አመራር ሰዎችን እያፈነ ገንዘብ ሲበስብ እንደነበር ተናግረዋል።

"ሰው ሲሸጡ የሚኖሩ ሰዎች አሉ፤ ኤርትራዊ መሸጥ ' ንብረት ' ነው የሚባለው ወርዷል ወይ ? ይባላል፤ ታፍንና ይዘህ 27 ወጣት አንድ ቤት ትዘጋና ቤተሰቦች አላቸው ውጭ ሀገር የሚባሉት ሰዎች አካውንት እየተጠየቀ እያንዳንዱ ሰው በትንሹ 4000 ዶላር እንዲያስገባ ተደርጎ (20 ሰው ካፈንክ 80 ሺህ ዶላር ታስገባለህ) በዚህ የውጭ አካውንት ከፍተው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን እየሸጡ፣ እያገቱ ገንዘብ እንዲሰበሰብ የሚያደርጉ አመራር የሚሰጡ ከፍተኛ አመራሮች አሉ" ብለዋል።

ይህ ተግባር መጀመሪያ በኤርትራውያን መጀመሩን ከዛም ወደ ትግራይ ተወላጆች መዞሩን ተናግረዋል።

እዚህ ጉዳይ ላይ ጥናት ተደርጎ አመራሮቹ ለህግ እንዲቀርቡ ሙከራ ቢደረግም ማቅረብ እንዳልተቻለና 2 ዓመት እንደሆነው ጠቁመዋል።

አቶ ጌታቸው "ይሄን የሚመራ የመረጃ መምሪያ ኃላፊ እርምጃ እንዲወሰድበት ወይ ከስራ እንዲነሳ ብለን ወስነን ስናበቃ ለማስፈጸም ኃላፊነት የሚሰጣቸው የፀጥታ አመራሮች አላስፈጸሙም" ሲሉ ተናግረዋል።

የፀጥታ አመራሮች በባህሪያቸው ጥፋት ያጠፋውም ያላጠፋውም የመተጋገዝ ባህሪ አላቸው ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ጌታቸው በወርቅ ንግድ ውስጥ ስላሉ አመራሮችም በዝርዝር ተናግረዋል።

"ወርቅ ንግድ ውስጥ የገባ ' ለትግራይ ነጻነት እስከመጨረሻው እሰዋለው ' እያለ የሚፎክር ጀነራል አለ አሁንም፤ እንዲህ አይነቱን የወርቅ ንግድ ውስጥ ነው ያለኸው ሊባል ይገባል" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው እነ ጀነራል ምግበ በወርቅ ንግድ ውስጥ ተሰማርተው እንደሚገኙ በስም ጠቅሰው ይፋ አድርገዋል።

"እነ ምግበ የሰሩት ጀግንነት የወጣት መስዕዋት መሰረት ተደርጎ የመጣ ጀግንነት ነው" ያሉት አቶ ጌታቸው "እነዛን ወጣቶች ለስደት በሚዳርግ ደረጃ ወደ ተራ የወርቅ ንግድ ገብተው ሲያበቁ የስርቆት ተግባራቸውን የትግራይ ግዛት አንድነት የማረጋገጥ አርገው እየገለጹ እንደገና ይሄን ወጣት ለሌላ መስዕዋትነት ሊዳርጉ እየተንቀሳቀሱ ነው" ብለዋል።

"እነ ኃይለስላሰም አሁን በትግራይ ህዝብ አንድነት ስም የትግራይን ወጣት ከኤርትራም ጋር ቢሆን አብሬ ለማገዶነት እንዳርገዋለው በሚል በጀግንነት ስም እየፎከረ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

እነ ምግበ ፣ እነ ኃይለስለሰ ፣ ኮሎኔል ተወልደን "በወንጀል የተነከሩ ሰዎች ናቸው" ብለዋቸዋል።

ድንገት ሰላም ቢፈጠር "ተጠያቂ እሆናለሁ፤ አደጋ ውስጥ እገባለሁ" ብለው ስለሚያስቡም ግርግር እንዲያልቅ አይፈልጉም ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

የትግራይን ህዝብ ለሌላ ጦርነት ለማስገባት እያሰቡ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ጌታቸው " የፌዴራል መንግሥት ድንገት ውጊያ ይገጥመናል " በሚል ስጋት ውጊያው ትግራይ ውስጥ እንዲካሄድ የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀይሶ እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል።

" ሰላም መፈጠር አለበት፤ በኢትዮጵያም በኤርትራም መካከል ጦርነት መፈጠር የለበትም፣ የኤርትራ ህዝብ ለአደጋ መዳረግ የለበትም እምነቴ ነው። ግን መምረጥ ካለብኝ የትግራይ ህዝብ ድጋሚ የጦር አውድማ የሚሆንበት ሁኔታ እስከመጨረሻው ድረስ እንዳይሆን እታገላለሁ " ብለዋል።

በዚህ ትግል እንቅፋት የሆኑት የወርቅ ንግድ ላይ የተሰማሩት ዘራፊዎች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።

" ' ግንባር አዛዥ ነኝ ' ይላል ወርቅ ሲዘርፍ ነው የሚውለው " ብለዋል።

"በ2014 ወጣቶች በየግንባሩ ሲተናነቁ በርቀት ዳባት፣ደባርቅ ፣ሊማሊሞ ሆኖ ውጊያ ይመራ የነበረ ሰው በተመሳሳይ ሰዓት በኤክስካቫተር ወርቅ እየቆፈረ ይሸጥ ነበር" ሲሉ ተደምጠዋል።

በዚህ የዝርፊያ ኔትዎርክ ፖለቲከኛውም እንዳለ ገልጸዋል።

ከዚህ ባለፈ አቶ ጌታቸው በመቶ ሚሊዮን ዘርፏል ስላሉት ኃለስላሰም ተናግረዋል።

" ኮምቦልቻ issue account ነበር፤ በዛ ሰዓት ጦርነት ላይ ገንዘብ ስለሚያስፈልገን ትክክለኛ ውሳኔ ነው የወሰነው የግል ባንኮች ሳንነካ የመንግሥት እንውሰድ ብለን ፓለቲካሊ ወሰንን እኔ እንደማውቀው 4 ቢሊዮን ብር ነበረው issue account ላይ ይሄን ከብሔራዊ ባንክ ማረጋገጥ ይቻላል ጊዜያዊ አስተዳደር ከሆንኩም በኃላ ወረቀት መጥቶልኛል ምን እንደተፈጠረ ባንኮች ውስጥ ግለጹልን የሚል እና issue account ውስጥ ያለውን ገንዘብ እንዲሰበስቡ ከተመደቡት ሰዎች መሃል አንዱ የግንባር አዛዥ የሚባለው ኃይለስላሰ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ነው የወሰደው ወደ አንድ ቢሊዮን አካባቢ ገንዘብ ነው የወሰደው እሱ ስር ተፍ ተፍ የሚሉ የሱ አገልጋዮች የተወሰነ ድርሻቸውን የወሰዱ አሉ " ብለዋል።

አብዛኛው ሰው ትግሉን ለትግራይ ህዝብ ካለው የህልውና ጥቅም አንጻር እንጂ "ገንዘብ አገኝበታለሁ" ብሎ አይደለም የተሳተፈው ሲሉ ተናግረዋል።

"እኔ በማውቀው ባረጋገጥኩት በሰነድ ጭምር እነ ኃይለ የወርቅ ማሽኖችን ሲያስገቡ ነው የሚውሉት" ብለዋል።

የፖለቲካ አመራሩም አብሮ የወርቅ ንግድ ውስጥ መሰማራቱን ጠቁመዋል።

ሰዎቹ ማሽን ሲያዝባቸው የፌዴራል ሰዎች ጋር እየተደዋወሉ "እናተን የመሰለ ሰው የለም" እያሉ እየተለማመጡ ማሽን ለማስለቀቅ እንደሚሞክሩ ገልጸዋል።

በጥናት " እገለ እግሌ 300 ሚሊዮን ወስዷል በቁጥጥር ስር ይዋል፣ እገሌ ይሄን ያህል ማሽነሪ ወስዷል በቁጥጥር ስር ይዋል እርምጃ ይወሰድ " ከተባለ 2 ዓመት እንደሆነው አመልክተዋል።

የቀረበውን የጥናት ዶክመት እነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) እንደሚያውቁት ጠቁመዋል።

ትግሉ ውስጥ ትልልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች ስም ሌሎችን ይዞ እንዳይጠፋና የውሸት አንድነት ለማስቀጠል ሲባል እምርጃ መውሰድ አልተቻለም ብለዋል።

"የመረረኝ ሰዓት እርምጃ እንዲወሰድ ዶክመንት አቅርቤም ተግባራዊ አልተደረግም" ብለዋል።

እነ ምግበን፣ እነ ኃይለስላሰን በስም ጠቅሰን መጠየቅ ስላልቻልን "ሁሉም የሰራዊት አመራሮች ዘርፈዋል" የሚል የጅምላ መልዕክት እያስተላለፍን ነው የመጣነው ይህ ውሸት ነው ብለዋል።

ተጠያቂነት እንዳይሰፍን የፖለቲካ መሪዎቹ እንቅፋት እንደሆኑ ይህን የሚያደርጉትም እነሱም ተጠያቂ ስለሆኑ እንደሆነ አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አድርገዋል።

አብዛኛው የሰራዊት አመራር ግን ሰላም ፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
🤔1.8K629😡200😭109😱106🕊86👏77🙏58💔34🥰29😢28



group-telegram.com/tikvahethiopia/96708
Create:
Last Update:

" እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ እስካሁን የታገስኩት ይበቃኛል " - አቶ ጌታቸው ረዳ

በትግራይ ያለው ህገወጥ የወርቅ ንግድ  ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ የጀመረ ሳይሆን በጦርነቱ ጊዜም ሳይቀር ሲሰራ የነበረ እንደሆነ የቀድሞው የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና የአሁኑ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አደረጉ።

አቶ ጌታቸው፤ "ብዙ ሰው የወርቅ ንግድ የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈራረምን በኃላ የጀመር ይመስለዋል" ያሉ ሲሆን ግን ጦርነቱም እየተካሄደ ንግዱ ነበር ብለዋል።

"እኔ የማምንበትን ትግል ነው ያካሄድኩት ብዬ አምናለሁ በዛ በማምንበት ትግል ውስጥ የትግራይን ህዝብ አጀንዳ ይዘው የታገሉ ብዙ የጦር መኮንኖች አሉ ለሰሩት ስራ ያለኝ ክብር በፍጹም አይቀንስም ግን ደግሞ ገና ገና ጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ይበላ በነበረበት ወቅት ሳይቀር ምሽግ ለመቆፈር ብለን የወሰድነው ኤክስካቫተር ወርቅ ለመልቀም ይጠቀሙበት የነበሩ አዛዦችም ነበሩ" ሲሉ አጋልጠዋል።

"ሲዋሹ በጣም ነው የሚገርመኝ" ያሉት አቶ ጌታቸው "እኔ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል እስካሁን የታገስኩትም ይበቃኛል" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው "የኤርትራን ሰራዊት እናፍርሰው" በሚል አላማ ዘመቻ የጀመረና ዘመቻውን የሚመራው አመራር ሰዎችን እያፈነ ገንዘብ ሲበስብ እንደነበር ተናግረዋል።

"ሰው ሲሸጡ የሚኖሩ ሰዎች አሉ፤ ኤርትራዊ መሸጥ ' ንብረት ' ነው የሚባለው ወርዷል ወይ ? ይባላል፤ ታፍንና ይዘህ 27 ወጣት አንድ ቤት ትዘጋና ቤተሰቦች አላቸው ውጭ ሀገር የሚባሉት ሰዎች አካውንት እየተጠየቀ እያንዳንዱ ሰው በትንሹ 4000 ዶላር እንዲያስገባ ተደርጎ (20 ሰው ካፈንክ 80 ሺህ ዶላር ታስገባለህ) በዚህ የውጭ አካውንት ከፍተው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን እየሸጡ፣ እያገቱ ገንዘብ እንዲሰበሰብ የሚያደርጉ አመራር የሚሰጡ ከፍተኛ አመራሮች አሉ" ብለዋል።

ይህ ተግባር መጀመሪያ በኤርትራውያን መጀመሩን ከዛም ወደ ትግራይ ተወላጆች መዞሩን ተናግረዋል።

እዚህ ጉዳይ ላይ ጥናት ተደርጎ አመራሮቹ ለህግ እንዲቀርቡ ሙከራ ቢደረግም ማቅረብ እንዳልተቻለና 2 ዓመት እንደሆነው ጠቁመዋል።

አቶ ጌታቸው "ይሄን የሚመራ የመረጃ መምሪያ ኃላፊ እርምጃ እንዲወሰድበት ወይ ከስራ እንዲነሳ ብለን ወስነን ስናበቃ ለማስፈጸም ኃላፊነት የሚሰጣቸው የፀጥታ አመራሮች አላስፈጸሙም" ሲሉ ተናግረዋል።

የፀጥታ አመራሮች በባህሪያቸው ጥፋት ያጠፋውም ያላጠፋውም የመተጋገዝ ባህሪ አላቸው ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ጌታቸው በወርቅ ንግድ ውስጥ ስላሉ አመራሮችም በዝርዝር ተናግረዋል።

"ወርቅ ንግድ ውስጥ የገባ ' ለትግራይ ነጻነት እስከመጨረሻው እሰዋለው ' እያለ የሚፎክር ጀነራል አለ አሁንም፤ እንዲህ አይነቱን የወርቅ ንግድ ውስጥ ነው ያለኸው ሊባል ይገባል" ብለዋል።

አቶ ጌታቸው እነ ጀነራል ምግበ በወርቅ ንግድ ውስጥ ተሰማርተው እንደሚገኙ በስም ጠቅሰው ይፋ አድርገዋል።

"እነ ምግበ የሰሩት ጀግንነት የወጣት መስዕዋት መሰረት ተደርጎ የመጣ ጀግንነት ነው" ያሉት አቶ ጌታቸው "እነዛን ወጣቶች ለስደት በሚዳርግ ደረጃ ወደ ተራ የወርቅ ንግድ ገብተው ሲያበቁ የስርቆት ተግባራቸውን የትግራይ ግዛት አንድነት የማረጋገጥ አርገው እየገለጹ እንደገና ይሄን ወጣት ለሌላ መስዕዋትነት ሊዳርጉ እየተንቀሳቀሱ ነው" ብለዋል።

"እነ ኃይለስላሰም አሁን በትግራይ ህዝብ አንድነት ስም የትግራይን ወጣት ከኤርትራም ጋር ቢሆን አብሬ ለማገዶነት እንዳርገዋለው በሚል በጀግንነት ስም እየፎከረ ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

እነ ምግበ ፣ እነ ኃይለስለሰ ፣ ኮሎኔል ተወልደን "በወንጀል የተነከሩ ሰዎች ናቸው" ብለዋቸዋል።

ድንገት ሰላም ቢፈጠር "ተጠያቂ እሆናለሁ፤ አደጋ ውስጥ እገባለሁ" ብለው ስለሚያስቡም ግርግር እንዲያልቅ አይፈልጉም ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

የትግራይን ህዝብ ለሌላ ጦርነት ለማስገባት እያሰቡ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ጌታቸው " የፌዴራል መንግሥት ድንገት ውጊያ ይገጥመናል " በሚል ስጋት ውጊያው ትግራይ ውስጥ እንዲካሄድ የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀይሶ እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል።

" ሰላም መፈጠር አለበት፤ በኢትዮጵያም በኤርትራም መካከል ጦርነት መፈጠር የለበትም፣ የኤርትራ ህዝብ ለአደጋ መዳረግ የለበትም እምነቴ ነው። ግን መምረጥ ካለብኝ የትግራይ ህዝብ ድጋሚ የጦር አውድማ የሚሆንበት ሁኔታ እስከመጨረሻው ድረስ እንዳይሆን እታገላለሁ " ብለዋል።

በዚህ ትግል እንቅፋት የሆኑት የወርቅ ንግድ ላይ የተሰማሩት ዘራፊዎች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።

" ' ግንባር አዛዥ ነኝ ' ይላል ወርቅ ሲዘርፍ ነው የሚውለው " ብለዋል።

"በ2014 ወጣቶች በየግንባሩ ሲተናነቁ በርቀት ዳባት፣ደባርቅ ፣ሊማሊሞ ሆኖ ውጊያ ይመራ የነበረ ሰው በተመሳሳይ ሰዓት በኤክስካቫተር ወርቅ እየቆፈረ ይሸጥ ነበር" ሲሉ ተደምጠዋል።

በዚህ የዝርፊያ ኔትዎርክ ፖለቲከኛውም እንዳለ ገልጸዋል።

ከዚህ ባለፈ አቶ ጌታቸው በመቶ ሚሊዮን ዘርፏል ስላሉት ኃለስላሰም ተናግረዋል።

" ኮምቦልቻ issue account ነበር፤ በዛ ሰዓት ጦርነት ላይ ገንዘብ ስለሚያስፈልገን ትክክለኛ ውሳኔ ነው የወሰነው የግል ባንኮች ሳንነካ የመንግሥት እንውሰድ ብለን ፓለቲካሊ ወሰንን እኔ እንደማውቀው 4 ቢሊዮን ብር ነበረው issue account ላይ ይሄን ከብሔራዊ ባንክ ማረጋገጥ ይቻላል ጊዜያዊ አስተዳደር ከሆንኩም በኃላ ወረቀት መጥቶልኛል ምን እንደተፈጠረ ባንኮች ውስጥ ግለጹልን የሚል እና issue account ውስጥ ያለውን ገንዘብ እንዲሰበስቡ ከተመደቡት ሰዎች መሃል አንዱ የግንባር አዛዥ የሚባለው ኃይለስላሰ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ነው የወሰደው ወደ አንድ ቢሊዮን አካባቢ ገንዘብ ነው የወሰደው እሱ ስር ተፍ ተፍ የሚሉ የሱ አገልጋዮች የተወሰነ ድርሻቸውን የወሰዱ አሉ " ብለዋል።

አብዛኛው ሰው ትግሉን ለትግራይ ህዝብ ካለው የህልውና ጥቅም አንጻር እንጂ "ገንዘብ አገኝበታለሁ" ብሎ አይደለም የተሳተፈው ሲሉ ተናግረዋል።

"እኔ በማውቀው ባረጋገጥኩት በሰነድ ጭምር እነ ኃይለ የወርቅ ማሽኖችን ሲያስገቡ ነው የሚውሉት" ብለዋል።

የፖለቲካ አመራሩም አብሮ የወርቅ ንግድ ውስጥ መሰማራቱን ጠቁመዋል።

ሰዎቹ ማሽን ሲያዝባቸው የፌዴራል ሰዎች ጋር እየተደዋወሉ "እናተን የመሰለ ሰው የለም" እያሉ እየተለማመጡ ማሽን ለማስለቀቅ እንደሚሞክሩ ገልጸዋል።

በጥናት " እገለ እግሌ 300 ሚሊዮን ወስዷል በቁጥጥር ስር ይዋል፣ እገሌ ይሄን ያህል ማሽነሪ ወስዷል በቁጥጥር ስር ይዋል እርምጃ ይወሰድ " ከተባለ 2 ዓመት እንደሆነው አመልክተዋል።

የቀረበውን የጥናት ዶክመት እነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) እንደሚያውቁት ጠቁመዋል።

ትግሉ ውስጥ ትልልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች ስም ሌሎችን ይዞ እንዳይጠፋና የውሸት አንድነት ለማስቀጠል ሲባል እምርጃ መውሰድ አልተቻለም ብለዋል።

"የመረረኝ ሰዓት እርምጃ እንዲወሰድ ዶክመንት አቅርቤም ተግባራዊ አልተደረግም" ብለዋል።

እነ ምግበን፣ እነ ኃይለስላሰን በስም ጠቅሰን መጠየቅ ስላልቻልን "ሁሉም የሰራዊት አመራሮች ዘርፈዋል" የሚል የጅምላ መልዕክት እያስተላለፍን ነው የመጣነው ይህ ውሸት ነው ብለዋል።

ተጠያቂነት እንዳይሰፍን የፖለቲካ መሪዎቹ እንቅፋት እንደሆኑ ይህን የሚያደርጉትም እነሱም ተጠያቂ ስለሆኑ እንደሆነ አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አድርገዋል።

አብዛኛው የሰራዊት አመራር ግን ሰላም ፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/96708

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Since January 2022, the SC has received a total of 47 complaints and enquiries on illegal investment schemes promoted through Telegram. These fraudulent schemes offer non-existent investment opportunities, promising very attractive and risk-free returns within a short span of time. They commonly offer unrealistic returns of as high as 1,000% within 24 hours or even within a few hours. Andrey, a Russian entrepreneur living in Brazil who, fearing retaliation, asked that NPR not use his last name, said Telegram has become one of the few places Russians can access independent news about the war. The SC urges the public to refer to the SC’s I nvestor Alert List before investing. The list contains details of unauthorised websites, investment products, companies and individuals. Members of the public who suspect that they have been approached by unauthorised firms or individuals offering schemes that promise unrealistic returns Pavel Durov, a billionaire who embraces an all-black wardrobe and is often compared to the character Neo from "the Matrix," funds Telegram through his personal wealth and debt financing. And despite being one of the world's most popular tech companies, Telegram reportedly has only about 30 employees who defer to Durov for most major decisions about the platform. "And that set off kind of a battle royale for control of the platform that Durov eventually lost," said Nathalie Maréchal of the Washington advocacy group Ranking Digital Rights.
from ca


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American