Telegram Group & Telegram Channel
" በመቶ ሚሊዮኖች ገንዘብ የሚገመት ንብረት ይዘን ለሁለት ቀናት ተሰልፈናል ፤ ስጋት ሊገለን ነዉ " - ቡናና ሸቀጦች ጭነዉ የተሰለፉ አሽከሪካሪዎች

➡️ " ሰልፉ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አማራጭ ስለሌለን እየተጠባበቅን ነዉ !! "


በሀገራችን አብዛኞቹ አከባቢዎች ባለዉ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ምክንያት በየማደያዉ ረጃጅም ሰልፎችን መመልከት የየዕለት ተግባር ሆኗል።

በተለይም አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ናፍጣ ለመቅዳት በየማደያዉ ለቀናት ተሰልፈዉ የሚጠባበቁ አሽከርካሪዎች ምን አይነት ጊዜ እንደሚያሳልፉና ሌላዉ ሰዉ አይረዳልንም ያሉትን ስሜት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አጋርተዋል።

ሁለት የተሳቢ አሽከርካሪዎች " እኛ የጫነዉ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣና ለሀገራችንም የዉጪ ምንዛሪን የሚያስገኝ የታጠበ ቡና ነዉ " ብለዋል።

" እኛ ጭንቀታችን ለሁለት ቀናት ተሰልፈን በተስፋ ከምንጠባበቀው ነዳጅ በላይ ተመርምሮና ተወግቶ ከቅምሻ ማዕከል በማሸጊያ ሽቦ ከታሰረ በኋላ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመጓዝ የተዘጋጀን ቡና ጭነን መሰለፉችን ነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።

" አንድ የታሸገ ሽቦ ቢትቆረጥ ከቀናት ሰልፍ በኋላ ወደ ተገላገልነዉ የቡና ጥራት ማስመርመሪያ ወረፋ ዳግም መመለስን ጨምሮ የመሰረቅ ስጋት እንዲሁም በቆየን ቁጥር በቡናዉ ጥራት ላይ ሊያጋጥም የሚችል የጥራት ጉድለት አደጋ ለከፍተኛ ስጋት ዳርጎናል " ብለዋል።

የእንስሳት ተዋፆ  ወተት፣ አይብና ቅቤ ጭኖ መሰለፉን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ " በወቅቱ ወደ አሰላ ካልደረስኩ ድርጅቴ ኪሳራዉ ከፍተኛ ነዉ " ሲል ገልጿል።

አንድ አሽከርካሪ ደግሞ ከቡታጅራ ወደ ሀዋሳ ተሳፋሪዎችን ይዞ ከመጣ በኋላ ለመመለስ በነዳጅ እጦት ምክንያት ለሶስት ቀናት መጉላላታቸዉን አስረድቷል።

ከአዲስ አበባ ሸቀጣ ሸቀጥ ጭኖ ወደ ዉሮ እየተጓዘ ላለፉት ሁለት ቀናት ነዳጅ በማጣቱ በሀዋሳ ከተማ በሁለት የተለያዩ ማደያዎች ተሰልፎ ማደሩን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ  በተስፋ የሚጠባበቁት ነዳጅ ደርሷቸዉ ቢቀዱ እንኳን በተያዘላቸው ቀን ለመድረስ ለአደጋ የተጋለጠ ጉዞ ለማድረግ እንደሚገደዱ ተናግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ አሽከርካሪዎችን ባነጋገረበት ወቅት በሀዋሳ ከተማ ደረቅ ቆሻሻ ከሚያነሱ ማህበራት መካከል የአንዱ ማህበር እንደሆነ የተነገረ የቆሻሻ መኪና ነዳጅ ጨርሶ ሰዓታትን አልፎ ከአንድ ቀን በላይ ይፈጃል በተባለዉ ሰልፍ መሃል የነበረ ሲሆን በአከባቢው መጥፎ ጠረን ተፈጥሮ በተነሳበት ተቃዉሞ በሰዉ ሃይል ተገፍቶ ነዳጅ ተቀድቶለት ተሸኝቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
😭785186🙏52🤔39🕊32😡31😱22💔18👏13😢11🥰5



group-telegram.com/tikvahethiopia/95628
Create:
Last Update:

" በመቶ ሚሊዮኖች ገንዘብ የሚገመት ንብረት ይዘን ለሁለት ቀናት ተሰልፈናል ፤ ስጋት ሊገለን ነዉ " - ቡናና ሸቀጦች ጭነዉ የተሰለፉ አሽከሪካሪዎች

➡️ " ሰልፉ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አማራጭ ስለሌለን እየተጠባበቅን ነዉ !! "


በሀገራችን አብዛኞቹ አከባቢዎች ባለዉ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ምክንያት በየማደያዉ ረጃጅም ሰልፎችን መመልከት የየዕለት ተግባር ሆኗል።

በተለይም አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ናፍጣ ለመቅዳት በየማደያዉ ለቀናት ተሰልፈዉ የሚጠባበቁ አሽከርካሪዎች ምን አይነት ጊዜ እንደሚያሳልፉና ሌላዉ ሰዉ አይረዳልንም ያሉትን ስሜት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አጋርተዋል።

ሁለት የተሳቢ አሽከርካሪዎች " እኛ የጫነዉ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣና ለሀገራችንም የዉጪ ምንዛሪን የሚያስገኝ የታጠበ ቡና ነዉ " ብለዋል።

" እኛ ጭንቀታችን ለሁለት ቀናት ተሰልፈን በተስፋ ከምንጠባበቀው ነዳጅ በላይ ተመርምሮና ተወግቶ ከቅምሻ ማዕከል በማሸጊያ ሽቦ ከታሰረ በኋላ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመጓዝ የተዘጋጀን ቡና ጭነን መሰለፉችን ነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።

" አንድ የታሸገ ሽቦ ቢትቆረጥ ከቀናት ሰልፍ በኋላ ወደ ተገላገልነዉ የቡና ጥራት ማስመርመሪያ ወረፋ ዳግም መመለስን ጨምሮ የመሰረቅ ስጋት እንዲሁም በቆየን ቁጥር በቡናዉ ጥራት ላይ ሊያጋጥም የሚችል የጥራት ጉድለት አደጋ ለከፍተኛ ስጋት ዳርጎናል " ብለዋል።

የእንስሳት ተዋፆ  ወተት፣ አይብና ቅቤ ጭኖ መሰለፉን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ " በወቅቱ ወደ አሰላ ካልደረስኩ ድርጅቴ ኪሳራዉ ከፍተኛ ነዉ " ሲል ገልጿል።

አንድ አሽከርካሪ ደግሞ ከቡታጅራ ወደ ሀዋሳ ተሳፋሪዎችን ይዞ ከመጣ በኋላ ለመመለስ በነዳጅ እጦት ምክንያት ለሶስት ቀናት መጉላላታቸዉን አስረድቷል።

ከአዲስ አበባ ሸቀጣ ሸቀጥ ጭኖ ወደ ዉሮ እየተጓዘ ላለፉት ሁለት ቀናት ነዳጅ በማጣቱ በሀዋሳ ከተማ በሁለት የተለያዩ ማደያዎች ተሰልፎ ማደሩን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ  በተስፋ የሚጠባበቁት ነዳጅ ደርሷቸዉ ቢቀዱ እንኳን በተያዘላቸው ቀን ለመድረስ ለአደጋ የተጋለጠ ጉዞ ለማድረግ እንደሚገደዱ ተናግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ አሽከርካሪዎችን ባነጋገረበት ወቅት በሀዋሳ ከተማ ደረቅ ቆሻሻ ከሚያነሱ ማህበራት መካከል የአንዱ ማህበር እንደሆነ የተነገረ የቆሻሻ መኪና ነዳጅ ጨርሶ ሰዓታትን አልፎ ከአንድ ቀን በላይ ይፈጃል በተባለዉ ሰልፍ መሃል የነበረ ሲሆን በአከባቢው መጥፎ ጠረን ተፈጥሮ በተነሳበት ተቃዉሞ በሰዉ ሃይል ተገፍቶ ነዳጅ ተቀድቶለት ተሸኝቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/95628

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Stocks dropped on Friday afternoon, as gains made earlier in the day on hopes for diplomatic progress between Russia and Ukraine turned to losses. Technology stocks were hit particularly hard by higher bond yields. So, uh, whenever I hear about Telegram, it’s always in relation to something bad. What gives? The channel appears to be part of the broader information war that has developed following Russia's invasion of Ukraine. The Kremlin has paid Russian TikTok influencers to push propaganda, according to a Vice News investigation, while ProPublica found that fake Russian fact check videos had been viewed over a million times on Telegram. Following this, Sebi, in an order passed in January 2022, established that the administrators of a Telegram channel having a large subscriber base enticed the subscribers to act upon recommendations that were circulated by those administrators on the channel, leading to significant price and volume impact in various scrips. The SC urges the public to refer to the SC’s I nvestor Alert List before investing. The list contains details of unauthorised websites, investment products, companies and individuals. Members of the public who suspect that they have been approached by unauthorised firms or individuals offering schemes that promise unrealistic returns
from hk


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American