" በመቶ ሚሊዮኖች ገንዘብ የሚገመት ንብረት ይዘን ለሁለት ቀናት ተሰልፈናል ፤ ስጋት ሊገለን ነዉ " - ቡናና ሸቀጦች ጭነዉ የተሰለፉ አሽከሪካሪዎች
➡️ " ሰልፉ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አማራጭ ስለሌለን እየተጠባበቅን ነዉ !! "
በሀገራችን አብዛኞቹ አከባቢዎች ባለዉ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ምክንያት በየማደያዉ ረጃጅም ሰልፎችን መመልከት የየዕለት ተግባር ሆኗል።
በተለይም አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ናፍጣ ለመቅዳት በየማደያዉ ለቀናት ተሰልፈዉ የሚጠባበቁ አሽከርካሪዎች ምን አይነት ጊዜ እንደሚያሳልፉና ሌላዉ ሰዉ አይረዳልንም ያሉትን ስሜት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አጋርተዋል።
ሁለት የተሳቢ አሽከርካሪዎች " እኛ የጫነዉ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣና ለሀገራችንም የዉጪ ምንዛሪን የሚያስገኝ የታጠበ ቡና ነዉ " ብለዋል።
" እኛ ጭንቀታችን ለሁለት ቀናት ተሰልፈን በተስፋ ከምንጠባበቀው ነዳጅ በላይ ተመርምሮና ተወግቶ ከቅምሻ ማዕከል በማሸጊያ ሽቦ ከታሰረ በኋላ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመጓዝ የተዘጋጀን ቡና ጭነን መሰለፉችን ነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።
" አንድ የታሸገ ሽቦ ቢትቆረጥ ከቀናት ሰልፍ በኋላ ወደ ተገላገልነዉ የቡና ጥራት ማስመርመሪያ ወረፋ ዳግም መመለስን ጨምሮ የመሰረቅ ስጋት እንዲሁም በቆየን ቁጥር በቡናዉ ጥራት ላይ ሊያጋጥም የሚችል የጥራት ጉድለት አደጋ ለከፍተኛ ስጋት ዳርጎናል " ብለዋል።
የእንስሳት ተዋፆ ወተት፣ አይብና ቅቤ ጭኖ መሰለፉን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ " በወቅቱ ወደ አሰላ ካልደረስኩ ድርጅቴ ኪሳራዉ ከፍተኛ ነዉ " ሲል ገልጿል።
አንድ አሽከርካሪ ደግሞ ከቡታጅራ ወደ ሀዋሳ ተሳፋሪዎችን ይዞ ከመጣ በኋላ ለመመለስ በነዳጅ እጦት ምክንያት ለሶስት ቀናት መጉላላታቸዉን አስረድቷል።
ከአዲስ አበባ ሸቀጣ ሸቀጥ ጭኖ ወደ ዉሮ እየተጓዘ ላለፉት ሁለት ቀናት ነዳጅ በማጣቱ በሀዋሳ ከተማ በሁለት የተለያዩ ማደያዎች ተሰልፎ ማደሩን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ በተስፋ የሚጠባበቁት ነዳጅ ደርሷቸዉ ቢቀዱ እንኳን በተያዘላቸው ቀን ለመድረስ ለአደጋ የተጋለጠ ጉዞ ለማድረግ እንደሚገደዱ ተናግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ አሽከርካሪዎችን ባነጋገረበት ወቅት በሀዋሳ ከተማ ደረቅ ቆሻሻ ከሚያነሱ ማህበራት መካከል የአንዱ ማህበር እንደሆነ የተነገረ የቆሻሻ መኪና ነዳጅ ጨርሶ ሰዓታትን አልፎ ከአንድ ቀን በላይ ይፈጃል በተባለዉ ሰልፍ መሃል የነበረ ሲሆን በአከባቢው መጥፎ ጠረን ተፈጥሮ በተነሳበት ተቃዉሞ በሰዉ ሃይል ተገፍቶ ነዳጅ ተቀድቶለት ተሸኝቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " ሰልፉ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አማራጭ ስለሌለን እየተጠባበቅን ነዉ !! "
በሀገራችን አብዛኞቹ አከባቢዎች ባለዉ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ምክንያት በየማደያዉ ረጃጅም ሰልፎችን መመልከት የየዕለት ተግባር ሆኗል።
በተለይም አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ናፍጣ ለመቅዳት በየማደያዉ ለቀናት ተሰልፈዉ የሚጠባበቁ አሽከርካሪዎች ምን አይነት ጊዜ እንደሚያሳልፉና ሌላዉ ሰዉ አይረዳልንም ያሉትን ስሜት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አጋርተዋል።
ሁለት የተሳቢ አሽከርካሪዎች " እኛ የጫነዉ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣና ለሀገራችንም የዉጪ ምንዛሪን የሚያስገኝ የታጠበ ቡና ነዉ " ብለዋል።
" እኛ ጭንቀታችን ለሁለት ቀናት ተሰልፈን በተስፋ ከምንጠባበቀው ነዳጅ በላይ ተመርምሮና ተወግቶ ከቅምሻ ማዕከል በማሸጊያ ሽቦ ከታሰረ በኋላ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመጓዝ የተዘጋጀን ቡና ጭነን መሰለፉችን ነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።
" አንድ የታሸገ ሽቦ ቢትቆረጥ ከቀናት ሰልፍ በኋላ ወደ ተገላገልነዉ የቡና ጥራት ማስመርመሪያ ወረፋ ዳግም መመለስን ጨምሮ የመሰረቅ ስጋት እንዲሁም በቆየን ቁጥር በቡናዉ ጥራት ላይ ሊያጋጥም የሚችል የጥራት ጉድለት አደጋ ለከፍተኛ ስጋት ዳርጎናል " ብለዋል።
የእንስሳት ተዋፆ ወተት፣ አይብና ቅቤ ጭኖ መሰለፉን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ " በወቅቱ ወደ አሰላ ካልደረስኩ ድርጅቴ ኪሳራዉ ከፍተኛ ነዉ " ሲል ገልጿል።
አንድ አሽከርካሪ ደግሞ ከቡታጅራ ወደ ሀዋሳ ተሳፋሪዎችን ይዞ ከመጣ በኋላ ለመመለስ በነዳጅ እጦት ምክንያት ለሶስት ቀናት መጉላላታቸዉን አስረድቷል።
ከአዲስ አበባ ሸቀጣ ሸቀጥ ጭኖ ወደ ዉሮ እየተጓዘ ላለፉት ሁለት ቀናት ነዳጅ በማጣቱ በሀዋሳ ከተማ በሁለት የተለያዩ ማደያዎች ተሰልፎ ማደሩን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ በተስፋ የሚጠባበቁት ነዳጅ ደርሷቸዉ ቢቀዱ እንኳን በተያዘላቸው ቀን ለመድረስ ለአደጋ የተጋለጠ ጉዞ ለማድረግ እንደሚገደዱ ተናግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ አሽከርካሪዎችን ባነጋገረበት ወቅት በሀዋሳ ከተማ ደረቅ ቆሻሻ ከሚያነሱ ማህበራት መካከል የአንዱ ማህበር እንደሆነ የተነገረ የቆሻሻ መኪና ነዳጅ ጨርሶ ሰዓታትን አልፎ ከአንድ ቀን በላይ ይፈጃል በተባለዉ ሰልፍ መሃል የነበረ ሲሆን በአከባቢው መጥፎ ጠረን ተፈጥሮ በተነሳበት ተቃዉሞ በሰዉ ሃይል ተገፍቶ ነዳጅ ተቀድቶለት ተሸኝቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
😭785❤186🙏52🤔39🕊32😡31😱22💔18👏13😢11🥰5
group-telegram.com/tikvahethiopia/95628
Create:
Last Update:
Last Update:
" በመቶ ሚሊዮኖች ገንዘብ የሚገመት ንብረት ይዘን ለሁለት ቀናት ተሰልፈናል ፤ ስጋት ሊገለን ነዉ " - ቡናና ሸቀጦች ጭነዉ የተሰለፉ አሽከሪካሪዎች
➡️ " ሰልፉ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አማራጭ ስለሌለን እየተጠባበቅን ነዉ !! "
በሀገራችን አብዛኞቹ አከባቢዎች ባለዉ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ምክንያት በየማደያዉ ረጃጅም ሰልፎችን መመልከት የየዕለት ተግባር ሆኗል።
በተለይም አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ናፍጣ ለመቅዳት በየማደያዉ ለቀናት ተሰልፈዉ የሚጠባበቁ አሽከርካሪዎች ምን አይነት ጊዜ እንደሚያሳልፉና ሌላዉ ሰዉ አይረዳልንም ያሉትን ስሜት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አጋርተዋል።
ሁለት የተሳቢ አሽከርካሪዎች " እኛ የጫነዉ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣና ለሀገራችንም የዉጪ ምንዛሪን የሚያስገኝ የታጠበ ቡና ነዉ " ብለዋል።
" እኛ ጭንቀታችን ለሁለት ቀናት ተሰልፈን በተስፋ ከምንጠባበቀው ነዳጅ በላይ ተመርምሮና ተወግቶ ከቅምሻ ማዕከል በማሸጊያ ሽቦ ከታሰረ በኋላ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመጓዝ የተዘጋጀን ቡና ጭነን መሰለፉችን ነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።
" አንድ የታሸገ ሽቦ ቢትቆረጥ ከቀናት ሰልፍ በኋላ ወደ ተገላገልነዉ የቡና ጥራት ማስመርመሪያ ወረፋ ዳግም መመለስን ጨምሮ የመሰረቅ ስጋት እንዲሁም በቆየን ቁጥር በቡናዉ ጥራት ላይ ሊያጋጥም የሚችል የጥራት ጉድለት አደጋ ለከፍተኛ ስጋት ዳርጎናል " ብለዋል።
የእንስሳት ተዋፆ ወተት፣ አይብና ቅቤ ጭኖ መሰለፉን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ " በወቅቱ ወደ አሰላ ካልደረስኩ ድርጅቴ ኪሳራዉ ከፍተኛ ነዉ " ሲል ገልጿል።
አንድ አሽከርካሪ ደግሞ ከቡታጅራ ወደ ሀዋሳ ተሳፋሪዎችን ይዞ ከመጣ በኋላ ለመመለስ በነዳጅ እጦት ምክንያት ለሶስት ቀናት መጉላላታቸዉን አስረድቷል።
ከአዲስ አበባ ሸቀጣ ሸቀጥ ጭኖ ወደ ዉሮ እየተጓዘ ላለፉት ሁለት ቀናት ነዳጅ በማጣቱ በሀዋሳ ከተማ በሁለት የተለያዩ ማደያዎች ተሰልፎ ማደሩን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ በተስፋ የሚጠባበቁት ነዳጅ ደርሷቸዉ ቢቀዱ እንኳን በተያዘላቸው ቀን ለመድረስ ለአደጋ የተጋለጠ ጉዞ ለማድረግ እንደሚገደዱ ተናግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ አሽከርካሪዎችን ባነጋገረበት ወቅት በሀዋሳ ከተማ ደረቅ ቆሻሻ ከሚያነሱ ማህበራት መካከል የአንዱ ማህበር እንደሆነ የተነገረ የቆሻሻ መኪና ነዳጅ ጨርሶ ሰዓታትን አልፎ ከአንድ ቀን በላይ ይፈጃል በተባለዉ ሰልፍ መሃል የነበረ ሲሆን በአከባቢው መጥፎ ጠረን ተፈጥሮ በተነሳበት ተቃዉሞ በሰዉ ሃይል ተገፍቶ ነዳጅ ተቀድቶለት ተሸኝቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " ሰልፉ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አማራጭ ስለሌለን እየተጠባበቅን ነዉ !! "
በሀገራችን አብዛኞቹ አከባቢዎች ባለዉ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ምክንያት በየማደያዉ ረጃጅም ሰልፎችን መመልከት የየዕለት ተግባር ሆኗል።
በተለይም አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ናፍጣ ለመቅዳት በየማደያዉ ለቀናት ተሰልፈዉ የሚጠባበቁ አሽከርካሪዎች ምን አይነት ጊዜ እንደሚያሳልፉና ሌላዉ ሰዉ አይረዳልንም ያሉትን ስሜት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አጋርተዋል።
ሁለት የተሳቢ አሽከርካሪዎች " እኛ የጫነዉ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣና ለሀገራችንም የዉጪ ምንዛሪን የሚያስገኝ የታጠበ ቡና ነዉ " ብለዋል።
" እኛ ጭንቀታችን ለሁለት ቀናት ተሰልፈን በተስፋ ከምንጠባበቀው ነዳጅ በላይ ተመርምሮና ተወግቶ ከቅምሻ ማዕከል በማሸጊያ ሽቦ ከታሰረ በኋላ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመጓዝ የተዘጋጀን ቡና ጭነን መሰለፉችን ነዉ " ሲሉ ገልጸዋል።
" አንድ የታሸገ ሽቦ ቢትቆረጥ ከቀናት ሰልፍ በኋላ ወደ ተገላገልነዉ የቡና ጥራት ማስመርመሪያ ወረፋ ዳግም መመለስን ጨምሮ የመሰረቅ ስጋት እንዲሁም በቆየን ቁጥር በቡናዉ ጥራት ላይ ሊያጋጥም የሚችል የጥራት ጉድለት አደጋ ለከፍተኛ ስጋት ዳርጎናል " ብለዋል።
የእንስሳት ተዋፆ ወተት፣ አይብና ቅቤ ጭኖ መሰለፉን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ " በወቅቱ ወደ አሰላ ካልደረስኩ ድርጅቴ ኪሳራዉ ከፍተኛ ነዉ " ሲል ገልጿል።
አንድ አሽከርካሪ ደግሞ ከቡታጅራ ወደ ሀዋሳ ተሳፋሪዎችን ይዞ ከመጣ በኋላ ለመመለስ በነዳጅ እጦት ምክንያት ለሶስት ቀናት መጉላላታቸዉን አስረድቷል።
ከአዲስ አበባ ሸቀጣ ሸቀጥ ጭኖ ወደ ዉሮ እየተጓዘ ላለፉት ሁለት ቀናት ነዳጅ በማጣቱ በሀዋሳ ከተማ በሁለት የተለያዩ ማደያዎች ተሰልፎ ማደሩን የነገረን ሌላኛው አሽከርካሪ በተስፋ የሚጠባበቁት ነዳጅ ደርሷቸዉ ቢቀዱ እንኳን በተያዘላቸው ቀን ለመድረስ ለአደጋ የተጋለጠ ጉዞ ለማድረግ እንደሚገደዱ ተናግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተዘዋውሮ አሽከርካሪዎችን ባነጋገረበት ወቅት በሀዋሳ ከተማ ደረቅ ቆሻሻ ከሚያነሱ ማህበራት መካከል የአንዱ ማህበር እንደሆነ የተነገረ የቆሻሻ መኪና ነዳጅ ጨርሶ ሰዓታትን አልፎ ከአንድ ቀን በላይ ይፈጃል በተባለዉ ሰልፍ መሃል የነበረ ሲሆን በአከባቢው መጥፎ ጠረን ተፈጥሮ በተነሳበት ተቃዉሞ በሰዉ ሃይል ተገፍቶ ነዳጅ ተቀድቶለት ተሸኝቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/95628