Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር ተፈተዋል " - ቤተሰቦች ከቀናት በፊት ከሰሞነኛዉ የጤና ባለሙያዎች እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እና ከአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ተወስደዉ ታስረዉ የነበሩ 3 ዶክተሮች በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር መፈታታቸዉን ቤተሰቦቻቸዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። " ባሳለፍነዉ ዐርብ ዕለት ' ለስብሰባ ትፈለጋላችሁ ' ተብለዉ በተወሰዱበት ነዉ እንዲታሰሩ የተደረገዉ…
🔈#የጤና_ባለሙያዎች

የጤና ባለሙያዎች ከዚህ ቀደም እስከ ግንቦት 3/2017 ዓ/ም ድረስ ለጠየቁት ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጣቸው ያ ካልሆነ በከፊል ስራ ለማቆም እንደሚገደዱ በጻፉት ደብዳቤ አሳውቀው ነበር።

በዚህም ዛሬ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ባሉ የጤና ተቋማት ወደ ስራ ያልገቡ እንዳሉ ይህም በመሆኑ ተቋማቱ ወደ ስራ እንዲመለሱ ማስጠንቀቂያ ሲለጥፉ እንደነበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" ጥያቄዎቻችን ምላሽ አልተሰጣቸውም " በማለት ስራ ያልገቡ ባለሙያዎች እስከ ግንቦት 9 ይቆያል ያሉት ከፊል የስራ ማቆም እንቅስቃሴ ፦
- የአዋቂ የድንገተኛ ህክምና ክፍል
- የህፃናት ድንገተኛ ክፍል
- ከድንገተኛ ክፍል ጋር ተያይዘው የሚሰጡ አገልግሎቶች እነዚህም የድንገተኛ ክፍል መድሃኒት ቤት እና ላቦራቶሪ
- የማዋለጃ ክፍል
- ፅኑ ህሙማን ክፍል (የጨቅላ እና የአዋቂዎች)
- የድንገተኛ ቀዶ ህክምና ክፍል የሚሰሩትን አይመለከትም ሲሉ ተናግረዋል።

" ከግንቦት 10 በኃለ ግን ምላሽ ካልተሰጠን ሙሉ በሙሉ እናቆማለን " ሲሉም ገልጸዋል።

" የእኛ እንቅስቃሴ አንዳችም የፖለቲካ ሆነ ከፖለቲከኞች ጋር የሚያይዘ አይደለም። ታዋቂም ሰዎች ሆኑ ማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚያራምዱ ሰዎችም እጃቸውን እንዲያነሱ ደጋግመን አሳስበናል። ሀገራችንን ህዝባችንን እንወዳለን ሰላምም እንድትሆን ነው የምንፈልገው ነገር ግን ዓመታት ያለፋቸው ጥያቄዎች መልስ ይሰጥባቸው ፤ ሁሌ ሽንገላና ማታለያ ይቁም " ብለዋል።

ጤና ባለሙያዎቹ ፥ " ያሉብን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በግልጽ ይታወቃሉ መፍትሄው ላይ ቁጭ ብለን እንነጋገርባቸውና ቁርጥ ያለ ዘላቂ መፍትሄ ይሰጠን። ቢመረን ፤ ኑሮውም ከአቅማችን በላይ ቢሆንብን ፣ ቤተሰብ ማስተዳደር ቀርቶ ጭራሽ ሸክም ወደመሆን በመሸጋገራችን ፤ ድካማችንን እንቅፍል ማጣታችንን የሚመጥን ነገር ሳናገኝ በመቅረታችን ነው እጅጉንም ቢከፋን ቢመረን ነው ወደዚህ እንቅስቃሴ የገባነው እንጂ ለማንም የፖለቲካ አጀንዳ ማራመጃ ለዩትዩብና ሚዲያ መነገጃ ለመሆን አይደለም። በእኛ ስም ፖለቲካ ለሚነግዱትም ተውን በለን ነገራቸዋል " ሲሉ አክለዋል።

ጤና ባለሙያዎቹ " ያሉብንን ችግሮች በይፋ ደጋግመን ጠይቀን ምላሽ ለመስጠት እስካሁን ድረስ ብቅ ያለ አካል የለም " ሲሉ ተናግረው አሁንም ጥያቄዎቻችንን በድጋሚ እናቀርባለን ሲሉ ገልጸዋል።

" ለጤና ሚኒስቴር ያቀረብናቸው ጥያቄዎቻችን ፦

1. የኢትዮጽያ ጤና ሚኒስቴር ዘመኑን በማይዋጅ አሰራር እየበዘበዘን ነው። የደመወዝ ክፍያን ከምስራቅ አፍሪቃ ሃገራት ተሞክሮ በመነሳት በአማካይ 1000$ (አንድ ሺ ዶላር) በወር ክፍያ ይጀምርልን። የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በሚያስቀምጠው ምክረ ሃሳብ መሰረት የስራ ሰዓት 45 ሰዓት በሳምንት ይገደብ ከዛ በላይ ለሆነውም ተመጣጣኝ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ይፈጸም።

2. ጤና ሚኒስቴር ለእኛ ለባለሙያዎቹ ተገቢውን የሆነ የቤት ኪራይ ፣ የተጋላጭነት እንዲሁም የማበረታቻ አበል ላይ አስቸኳይ ማስተካከያ ያድረግልን። በሥራ ላይ ሳሉ በበሽታ ለተጠቁ ባለሙያዎች ደግሞ ተጨማሪ ካሳ ይስጥልን።

3. እንደማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ በመታወቂያችን የነጻ ትራስፖርት ተጠቃሚ እንሁን አልያም ገበያውን ያማከለ የትራንስፖርት አበል ይታሰብልን። እንዲሁም ባለሙያው ከቀረጥ ነፃ መኪና አስገብቶ እንዲገለገል ጤና ሚኒስቴር መንግስትን ይጠይቅልን።

4. የትርፍ ሰዐት ክፍያ በሁሉም ጤና ተቋማት ላይ ህግን መሰረት አድርጎ በተመሳሳይ ይሰራ፤ ጊዜውን ጠብቆም ይከፈለን። ክፍያ ከዓመት በላይ በማዘግየት ጤና ባለሞያውን የሚበድሉ ተቋማት ላይ አስቸኳይ እርምጃ ይወሰድ።

5. መብታችንን እንዲሁም የሰራንበትን ዋጋ እንዳንጠይቅ በማሰር፣ በማሰቃየት፣ በማሸማቀቅ እና በማስፈራራት ከህግ አግባብ ውጪ በሆነ መልኩ ባለሙያን ለእንግልት እየዳረጉ ያሉ የጤና ተቋማት እና የመንግስት ሃላፊዎች ላይ ምርመራ ተካሂዶ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰደ ጤና ሚኒስቴር ኃላፊነቱን ይወጣልን።

6. ጤና ሚኒስቴር ለሁሉም የጤና ባለሙያዎች እና ቤተሰቦቻችን በሁሉም የመንግስትም ሆነ የግል የጤና ተቋማት ላይ የነፃ ሕክምና አገልግሎት ያስጀምር። ውጪ ሄደው መታከም ላለባቸው ባለሙያዎችም ግማሽ ወጪ ይሸፍን የኑሮ ግሽበትን ያማከለ ድጋፍ ያድርግልን።

7. ባለሙያዎች በሚስሩበት አካባቢ የቤት ወይም የማህበር መስርያ ቦታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አልያም በረጅም ግዜ ክፍያ ቤት የሚገዙበትን መንገድ ይመቻች።

8. ሚኒስቴሩ በስራ ቦታቸን ላይ ሰላማዊ መስተጋብር እና ደህንነቱ የተጠበቀ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲሁም የስራ አካባቢ እንዲፈጠር፣ በምንም መልኩ አግባብነት የሌለውን የጤና ባለሙያዎች ሞትንም እምርሮ ይታገልም መመርያም አውጥቶ ተፈፃሚነቱን ይከታተል።

9. የህክምና እውቀቱ ሆነ ሙያው በሌላቸው የሚዲያ ሰዎች በባለሙያው ላይ በሚነሱ አሉባልታና የሐሰት ክሶች ምክንያት ማህበረሰባችን በጤና ባለሙያ ላይ ያለውን እምነት እንዲሸረሸር ተደርጓል። እንዲህ ያለውን ግድየለሽ ተግባር የሚፈፅሙና ማስረጃ የሌለው የሐሰት ዜና የሚያሰራጩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ይደረግ።

10. እኛ ባለሙያዎች ለአለምአቀፍ ገበያ ብቁነታችንን የምናረጋግጥበት ዓለም አቀፍ የፈተና ማዕከላት / USMLE EXAM CENTER, NCLEX EXAM CENTER, PLAB, DHA, AMC / ከዓመት በፊት ቃል በተገባልን መሰረት ጤና ሚኒስቴር በሀገር ውስጥ ያቋቋምልን።

11. በሁሉም ጤና ተቋማት ላይ የሚታየው የአመራር ምርጫ በሹመት መሆኑ ከጤናው ዘርፍ የማይጠበቅ በመሆኑ ይሄ አሰራር አስቀርታቹ በእውቀት እና በውድድር እንዲሆን አድርጉት ፤ አሰራሩንም አዘምኑት።

12. የህክምና ዘርፍ ከሲቪል ሰርቪስ ማዕቀፍ እንዲወጣ በማድረግ ውስናችሁ አሳውቁን ፤ እራሱን ችሎ በቦርድ እንዲተዳደር ኃላፊነታችሁን ተወጡልን።

የሚሉ ናቸው " ብለዋል።

ጤና ሚኒስቴር ለተጠየቁት ለእነዚህ ግልጽ የሆኑ ጥያቄዎች ዙሪያ ጥምጥም መሄድ ሳያስፈልገው 1... 2 ... 3 እያለ በግልጽ ይመልሳቸው ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎቹ ላነሷቸው ጥያቄዎች ከጤና ሚኒስቴር በኩል ማብራሪያ ካገኘ ይዞ ይቀርባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.67K👏421🙏57🤔23😡23😢22🥰13🕊13😭12💔6😱5



group-telegram.com/tikvahethiopia/96711
Create:
Last Update:

🔈#የጤና_ባለሙያዎች

የጤና ባለሙያዎች ከዚህ ቀደም እስከ ግንቦት 3/2017 ዓ/ም ድረስ ለጠየቁት ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጣቸው ያ ካልሆነ በከፊል ስራ ለማቆም እንደሚገደዱ በጻፉት ደብዳቤ አሳውቀው ነበር።

በዚህም ዛሬ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ባሉ የጤና ተቋማት ወደ ስራ ያልገቡ እንዳሉ ይህም በመሆኑ ተቋማቱ ወደ ስራ እንዲመለሱ ማስጠንቀቂያ ሲለጥፉ እንደነበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" ጥያቄዎቻችን ምላሽ አልተሰጣቸውም " በማለት ስራ ያልገቡ ባለሙያዎች እስከ ግንቦት 9 ይቆያል ያሉት ከፊል የስራ ማቆም እንቅስቃሴ ፦
- የአዋቂ የድንገተኛ ህክምና ክፍል
- የህፃናት ድንገተኛ ክፍል
- ከድንገተኛ ክፍል ጋር ተያይዘው የሚሰጡ አገልግሎቶች እነዚህም የድንገተኛ ክፍል መድሃኒት ቤት እና ላቦራቶሪ
- የማዋለጃ ክፍል
- ፅኑ ህሙማን ክፍል (የጨቅላ እና የአዋቂዎች)
- የድንገተኛ ቀዶ ህክምና ክፍል የሚሰሩትን አይመለከትም ሲሉ ተናግረዋል።

" ከግንቦት 10 በኃለ ግን ምላሽ ካልተሰጠን ሙሉ በሙሉ እናቆማለን " ሲሉም ገልጸዋል።

" የእኛ እንቅስቃሴ አንዳችም የፖለቲካ ሆነ ከፖለቲከኞች ጋር የሚያይዘ አይደለም። ታዋቂም ሰዎች ሆኑ ማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚያራምዱ ሰዎችም እጃቸውን እንዲያነሱ ደጋግመን አሳስበናል። ሀገራችንን ህዝባችንን እንወዳለን ሰላምም እንድትሆን ነው የምንፈልገው ነገር ግን ዓመታት ያለፋቸው ጥያቄዎች መልስ ይሰጥባቸው ፤ ሁሌ ሽንገላና ማታለያ ይቁም " ብለዋል።

ጤና ባለሙያዎቹ ፥ " ያሉብን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በግልጽ ይታወቃሉ መፍትሄው ላይ ቁጭ ብለን እንነጋገርባቸውና ቁርጥ ያለ ዘላቂ መፍትሄ ይሰጠን። ቢመረን ፤ ኑሮውም ከአቅማችን በላይ ቢሆንብን ፣ ቤተሰብ ማስተዳደር ቀርቶ ጭራሽ ሸክም ወደመሆን በመሸጋገራችን ፤ ድካማችንን እንቅፍል ማጣታችንን የሚመጥን ነገር ሳናገኝ በመቅረታችን ነው እጅጉንም ቢከፋን ቢመረን ነው ወደዚህ እንቅስቃሴ የገባነው እንጂ ለማንም የፖለቲካ አጀንዳ ማራመጃ ለዩትዩብና ሚዲያ መነገጃ ለመሆን አይደለም። በእኛ ስም ፖለቲካ ለሚነግዱትም ተውን በለን ነገራቸዋል " ሲሉ አክለዋል።

ጤና ባለሙያዎቹ " ያሉብንን ችግሮች በይፋ ደጋግመን ጠይቀን ምላሽ ለመስጠት እስካሁን ድረስ ብቅ ያለ አካል የለም " ሲሉ ተናግረው አሁንም ጥያቄዎቻችንን በድጋሚ እናቀርባለን ሲሉ ገልጸዋል።

" ለጤና ሚኒስቴር ያቀረብናቸው ጥያቄዎቻችን ፦

1. የኢትዮጽያ ጤና ሚኒስቴር ዘመኑን በማይዋጅ አሰራር እየበዘበዘን ነው። የደመወዝ ክፍያን ከምስራቅ አፍሪቃ ሃገራት ተሞክሮ በመነሳት በአማካይ 1000$ (አንድ ሺ ዶላር) በወር ክፍያ ይጀምርልን። የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በሚያስቀምጠው ምክረ ሃሳብ መሰረት የስራ ሰዓት 45 ሰዓት በሳምንት ይገደብ ከዛ በላይ ለሆነውም ተመጣጣኝ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ይፈጸም።

2. ጤና ሚኒስቴር ለእኛ ለባለሙያዎቹ ተገቢውን የሆነ የቤት ኪራይ ፣ የተጋላጭነት እንዲሁም የማበረታቻ አበል ላይ አስቸኳይ ማስተካከያ ያድረግልን። በሥራ ላይ ሳሉ በበሽታ ለተጠቁ ባለሙያዎች ደግሞ ተጨማሪ ካሳ ይስጥልን።

3. እንደማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ በመታወቂያችን የነጻ ትራስፖርት ተጠቃሚ እንሁን አልያም ገበያውን ያማከለ የትራንስፖርት አበል ይታሰብልን። እንዲሁም ባለሙያው ከቀረጥ ነፃ መኪና አስገብቶ እንዲገለገል ጤና ሚኒስቴር መንግስትን ይጠይቅልን።

4. የትርፍ ሰዐት ክፍያ በሁሉም ጤና ተቋማት ላይ ህግን መሰረት አድርጎ በተመሳሳይ ይሰራ፤ ጊዜውን ጠብቆም ይከፈለን። ክፍያ ከዓመት በላይ በማዘግየት ጤና ባለሞያውን የሚበድሉ ተቋማት ላይ አስቸኳይ እርምጃ ይወሰድ።

5. መብታችንን እንዲሁም የሰራንበትን ዋጋ እንዳንጠይቅ በማሰር፣ በማሰቃየት፣ በማሸማቀቅ እና በማስፈራራት ከህግ አግባብ ውጪ በሆነ መልኩ ባለሙያን ለእንግልት እየዳረጉ ያሉ የጤና ተቋማት እና የመንግስት ሃላፊዎች ላይ ምርመራ ተካሂዶ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰደ ጤና ሚኒስቴር ኃላፊነቱን ይወጣልን።

6. ጤና ሚኒስቴር ለሁሉም የጤና ባለሙያዎች እና ቤተሰቦቻችን በሁሉም የመንግስትም ሆነ የግል የጤና ተቋማት ላይ የነፃ ሕክምና አገልግሎት ያስጀምር። ውጪ ሄደው መታከም ላለባቸው ባለሙያዎችም ግማሽ ወጪ ይሸፍን የኑሮ ግሽበትን ያማከለ ድጋፍ ያድርግልን።

7. ባለሙያዎች በሚስሩበት አካባቢ የቤት ወይም የማህበር መስርያ ቦታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አልያም በረጅም ግዜ ክፍያ ቤት የሚገዙበትን መንገድ ይመቻች።

8. ሚኒስቴሩ በስራ ቦታቸን ላይ ሰላማዊ መስተጋብር እና ደህንነቱ የተጠበቀ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲሁም የስራ አካባቢ እንዲፈጠር፣ በምንም መልኩ አግባብነት የሌለውን የጤና ባለሙያዎች ሞትንም እምርሮ ይታገልም መመርያም አውጥቶ ተፈፃሚነቱን ይከታተል።

9. የህክምና እውቀቱ ሆነ ሙያው በሌላቸው የሚዲያ ሰዎች በባለሙያው ላይ በሚነሱ አሉባልታና የሐሰት ክሶች ምክንያት ማህበረሰባችን በጤና ባለሙያ ላይ ያለውን እምነት እንዲሸረሸር ተደርጓል። እንዲህ ያለውን ግድየለሽ ተግባር የሚፈፅሙና ማስረጃ የሌለው የሐሰት ዜና የሚያሰራጩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ይደረግ።

10. እኛ ባለሙያዎች ለአለምአቀፍ ገበያ ብቁነታችንን የምናረጋግጥበት ዓለም አቀፍ የፈተና ማዕከላት / USMLE EXAM CENTER, NCLEX EXAM CENTER, PLAB, DHA, AMC / ከዓመት በፊት ቃል በተገባልን መሰረት ጤና ሚኒስቴር በሀገር ውስጥ ያቋቋምልን።

11. በሁሉም ጤና ተቋማት ላይ የሚታየው የአመራር ምርጫ በሹመት መሆኑ ከጤናው ዘርፍ የማይጠበቅ በመሆኑ ይሄ አሰራር አስቀርታቹ በእውቀት እና በውድድር እንዲሆን አድርጉት ፤ አሰራሩንም አዘምኑት።

12. የህክምና ዘርፍ ከሲቪል ሰርቪስ ማዕቀፍ እንዲወጣ በማድረግ ውስናችሁ አሳውቁን ፤ እራሱን ችሎ በቦርድ እንዲተዳደር ኃላፊነታችሁን ተወጡልን።

የሚሉ ናቸው " ብለዋል።

ጤና ሚኒስቴር ለተጠየቁት ለእነዚህ ግልጽ የሆኑ ጥያቄዎች ዙሪያ ጥምጥም መሄድ ሳያስፈልገው 1... 2 ... 3 እያለ በግልጽ ይመልሳቸው ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎቹ ላነሷቸው ጥያቄዎች ከጤና ሚኒስቴር በኩል ማብራሪያ ካገኘ ይዞ ይቀርባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA









Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/96711

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The news also helped traders look past another report showing decades-high inflation and shake off some of the volatility from recent sessions. The Bureau of Labor Statistics' February Consumer Price Index (CPI) this week showed another surge in prices even before Russia escalated its attacks in Ukraine. The headline CPI — soaring 7.9% over last year — underscored the sticky inflationary pressures reverberating across the U.S. economy, with everything from groceries to rents and airline fares getting more expensive for everyday consumers. Telegram does offer end-to-end encrypted communications through Secret Chats, but this is not the default setting. Standard conversations use the MTProto method, enabling server-client encryption but with them stored on the server for ease-of-access. This makes using Telegram across multiple devices simple, but also means that the regular Telegram chats you’re having with folks are not as secure as you may believe. "There are several million Russians who can lift their head up from propaganda and try to look for other sources, and I'd say that most look for it on Telegram," he said. Also in the latest update is the ability for users to create a unique @username from the Settings page, providing others with an easy way to contact them via Search or their t.me/username link without sharing their phone number. You may recall that, back when Facebook started changing WhatsApp’s terms of service, a number of news outlets reported on, and even recommended, switching to Telegram. Pavel Durov even said that users should delete WhatsApp “unless you are cool with all of your photos and messages becoming public one day.” But Telegram can’t be described as a more-secure version of WhatsApp.
from hk


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American