Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሂጃብሂጃብ #አክሱም " ተከሳሾች የሰጡት አስተዳደራዊ ትእዛዝ መዝገቡ እልባት እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ #እንዳይተገበር ለጊዜው በእግድ እንዲቆይ ታዟል " - ፍርድ ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ክልከላ አድርገዋል በተባሉት አካላት ላይ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ህጋዊ ክስ…
#Update

🧕" የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ በመጣስ አሁንም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች / ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ ከልክሏል "  - የተማሪዎች ቤተሰቦች

👉 " የተጣሰ የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ የለም ፤ የትምህርት ህግ እና ደንብ ያከበሩ ተማሪዎች ወደ ክፍል ገብተው መማር ጀምረዋል ፤ ቀሪዎቹ እንዲመለሱ ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ ነን " -  የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር

የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም በፃፈው የእግድ ትእዛዝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው እንዲማሩ ፤ በክልከላ የተሳተፉ አካላት ለጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ቢያዝም ተግባራዊ አልሆነም ብለዋል የተማሪዎች ቤተሰቦች።

የተማሪ ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ (መቐለ) በሰጡት አስተያየት ፤ " የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር በተያያዘ በአክሱም ከተማ ፍርድ  ቤት በኩል በ5 አካላት ላይ የእግድ ደብዳቤ ቢያፅፍም ተግባራዊ አልሆነም ተጥሷል " ብለዋል። 

የእግድ ትእዛዙን ከጣሱት አንዱ የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሆኑን የጠቀሱት የተማሪ ቤተሰቦች ፤ " ትምህርት ቤቱ የእግድ ትእዛዙን በመጣስ ጥር 7 እና 8/2017 ዓ.ም ተማሪዎቹ ክፍል ገብተው እንዳይማሩ በማድረግ ተደራራቢ ጥፋቶች እየፈፀመ ነው " ሲሉ ከሰዋል። 

አስተያየት ሰጪዎቹ  " ከህግ በላይ መሆን ልክ አይደለም የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና የሃይማኖት መብት ይከበር " ሲሉ ምሬታቸው ገልፀዋል። 

በተማሪዎች ቤተሰቦች በኩል ለቀረበው አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ምላሽ የሰጡት የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ርእሰ መምህር ስዩም ካሕሳይ ፥ " ትምህርት ቤታችን ' የፍርድ ቤት እግድ እና ትእዛዝ በመጣስ ተማሪዎቹ እንዳይማሩ ከልክሏል ' የሚባለው ስህተት ነው " ብለዋል።   

" ለተማሪ ሴት ልጆቻችን በቅርብ እና በሩቅ ሆኖው ' እንቆረቆራለን ' ከሚሉት በላይ እናስብላቸዋለን " ያሉት ርእሰ መምህሩ " አሁንም ጉዳዩ ከሚገባው በላይ ማጋነን እና ማቀጣጠል እንዲሁም ለፓለቲካዊ ፍጆታ ማዋል ለአገር እና ህዝብ አይጠቅምም " ሲሉ አብራርተዋል።  

" የትምህርት ቤታችን አስተዳደር የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና እግድ ሳይጠብቅ የተፈጠረው አለመግባባት እንዲፈታ ሌት ተቀን በመስራት ላይ እንገኛለን " ሲሉ ገልጸው " የፍርድ ቤቱ ቃል አክብረን የትምህርት ቤቱ መምሪያ እና ደንብ በመጠበቅ ጥቂት የማይባሉ ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው መልሰናል የተቀሩት ለመመለስ ደግሞ በማያቋርጥ ጥረት ላይ እንገኛለን " ብለዋል።

" ከ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ የቀሩት እንዲካተቱ ከሚመለከታቸው አካላት ተከታታይ ስራዎች እየሰራን " ሲሉ አክለዋል።   

ከሂጃብ መልበስ ጋር ተያይዞ ከ2017 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲቀሩ  የሆኑት 159 የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጉዳይ ክልላዊ እና አገራዊ አጀንዳ ከመሆን በዘለለ በህግ እንዲታይ ወደ ፍርድ አምርቷል።

ከሂጃብ አጠቃቀም ክልከላ ጋር በተያያዘ ተሳታፊ ናቸው በተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ 5 አካላት ለጥር 16/2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ፤ ጎን ለጎን ደግሞ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም አዟል።  

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ዛሬ ጥር 8/2017 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ በፃፈው ደብዳቤ ፤ የሂጃብ መልበስ ክልከላው እንዲያነሳ አሳውቋል።

በተያያዘ መረጃ ከሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ጋር ተያይዞ ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ መከልከሉ ለመቃወም የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለዓርብ ጥር 9/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ እንዲካሄድ የጠራው እና የተፈቀደ ሰላማዊ ሰልፍ የጥምቀት በዓል ዋዜማ በመሆኑ ምክንያት ወደ ጥር 13/2017 ዓ.ም ማዘዋወሩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ  ከምክር ቤቱ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
1😡1.05K310👏118😭79🕊43🥰29🤔28😢24😱16🙏10



group-telegram.com/tikvahethiopia/93781
Create:
Last Update:

#Update

🧕" የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ በመጣስ አሁንም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች / ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ ከልክሏል "  - የተማሪዎች ቤተሰቦች

👉 " የተጣሰ የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ የለም ፤ የትምህርት ህግ እና ደንብ ያከበሩ ተማሪዎች ወደ ክፍል ገብተው መማር ጀምረዋል ፤ ቀሪዎቹ እንዲመለሱ ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ ነን " -  የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር

የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም በፃፈው የእግድ ትእዛዝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው እንዲማሩ ፤ በክልከላ የተሳተፉ አካላት ለጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ቢያዝም ተግባራዊ አልሆነም ብለዋል የተማሪዎች ቤተሰቦች።

የተማሪ ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ (መቐለ) በሰጡት አስተያየት ፤ " የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር በተያያዘ በአክሱም ከተማ ፍርድ  ቤት በኩል በ5 አካላት ላይ የእግድ ደብዳቤ ቢያፅፍም ተግባራዊ አልሆነም ተጥሷል " ብለዋል። 

የእግድ ትእዛዙን ከጣሱት አንዱ የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሆኑን የጠቀሱት የተማሪ ቤተሰቦች ፤ " ትምህርት ቤቱ የእግድ ትእዛዙን በመጣስ ጥር 7 እና 8/2017 ዓ.ም ተማሪዎቹ ክፍል ገብተው እንዳይማሩ በማድረግ ተደራራቢ ጥፋቶች እየፈፀመ ነው " ሲሉ ከሰዋል። 

አስተያየት ሰጪዎቹ  " ከህግ በላይ መሆን ልክ አይደለም የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና የሃይማኖት መብት ይከበር " ሲሉ ምሬታቸው ገልፀዋል። 

በተማሪዎች ቤተሰቦች በኩል ለቀረበው አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ምላሽ የሰጡት የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ርእሰ መምህር ስዩም ካሕሳይ ፥ " ትምህርት ቤታችን ' የፍርድ ቤት እግድ እና ትእዛዝ በመጣስ ተማሪዎቹ እንዳይማሩ ከልክሏል ' የሚባለው ስህተት ነው " ብለዋል።   

" ለተማሪ ሴት ልጆቻችን በቅርብ እና በሩቅ ሆኖው ' እንቆረቆራለን ' ከሚሉት በላይ እናስብላቸዋለን " ያሉት ርእሰ መምህሩ " አሁንም ጉዳዩ ከሚገባው በላይ ማጋነን እና ማቀጣጠል እንዲሁም ለፓለቲካዊ ፍጆታ ማዋል ለአገር እና ህዝብ አይጠቅምም " ሲሉ አብራርተዋል።  

" የትምህርት ቤታችን አስተዳደር የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና እግድ ሳይጠብቅ የተፈጠረው አለመግባባት እንዲፈታ ሌት ተቀን በመስራት ላይ እንገኛለን " ሲሉ ገልጸው " የፍርድ ቤቱ ቃል አክብረን የትምህርት ቤቱ መምሪያ እና ደንብ በመጠበቅ ጥቂት የማይባሉ ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው መልሰናል የተቀሩት ለመመለስ ደግሞ በማያቋርጥ ጥረት ላይ እንገኛለን " ብለዋል።

" ከ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ የቀሩት እንዲካተቱ ከሚመለከታቸው አካላት ተከታታይ ስራዎች እየሰራን " ሲሉ አክለዋል።   

ከሂጃብ መልበስ ጋር ተያይዞ ከ2017 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲቀሩ  የሆኑት 159 የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጉዳይ ክልላዊ እና አገራዊ አጀንዳ ከመሆን በዘለለ በህግ እንዲታይ ወደ ፍርድ አምርቷል።

ከሂጃብ አጠቃቀም ክልከላ ጋር በተያያዘ ተሳታፊ ናቸው በተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ 5 አካላት ለጥር 16/2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ፤ ጎን ለጎን ደግሞ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም አዟል።  

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ዛሬ ጥር 8/2017 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ በፃፈው ደብዳቤ ፤ የሂጃብ መልበስ ክልከላው እንዲያነሳ አሳውቋል።

በተያያዘ መረጃ ከሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ጋር ተያይዞ ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ መከልከሉ ለመቃወም የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለዓርብ ጥር 9/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ እንዲካሄድ የጠራው እና የተፈቀደ ሰላማዊ ሰልፍ የጥምቀት በዓል ዋዜማ በመሆኑ ምክንያት ወደ ጥር 13/2017 ዓ.ም ማዘዋወሩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ  ከምክር ቤቱ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA







Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93781

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The company maintains that it cannot act against individual or group chats, which are “private amongst their participants,” but it will respond to requests in relation to sticker sets, channels and bots which are publicly available. During the invasion of Ukraine, Pavel Durov has wrestled with this issue a lot more prominently than he has before. Channels like Donbass Insider and Bellum Acta, as reported by Foreign Policy, started pumping out pro-Russian propaganda as the invasion began. So much so that the Ukrainian National Security and Defense Council issued a statement labeling which accounts are Russian-backed. Ukrainian officials, in potential violation of the Geneva Convention, have shared imagery of dead and captured Russian soldiers on the platform. In the past, it was noticed that through bulk SMSes, investors were induced to invest in or purchase the stocks of certain listed companies. Given the pro-privacy stance of the platform, it’s taken as a given that it’ll be used for a number of reasons, not all of them good. And Telegram has been attached to a fair few scandals related to terrorism, sexual exploitation and crime. Back in 2015, Vox described Telegram as “ISIS’ app of choice,” saying that the platform’s real use is the ability to use channels to distribute material to large groups at once. Telegram has acted to remove public channels affiliated with terrorism, but Pavel Durov reiterated that he had no business snooping on private conversations. Either way, Durov says that he withdrew his resignation but that he was ousted from his company anyway. Subsequently, control of the company was reportedly handed to oligarchs Alisher Usmanov and Igor Sechin, both allegedly close associates of Russian leader Vladimir Putin. "For Telegram, accountability has always been a problem, which is why it was so popular even before the full-scale war with far-right extremists and terrorists from all over the world," she told AFP from her safe house outside the Ukrainian capital.
from id


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American