Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኮሬ 🛑 “ አሁንም ግድያው እንደቀጠለ ነው። ዛሬም 3 ሰዎች በታጣቂዎች ተገድለዋል” - ኮሬ ዞን 🔵 “ ምንም መፍትሄ የሌለው ጉዳይ ነው የሆነው። ግድያና መፈናቀሉ ቀጥሏል” - በፌደራል ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የኮሬ ህዝብ ተወካይ ዛሬ (ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ/ም) ሦስት ንጹሐን ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል ከምዕራብ ጉጂ በተነሱ ታጣቂዎች መገዳላቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኮሬ ዞን አስተዳደር ለቲክቫህ…
#ኮሬ

🛑 " ከትላንትና በስቲያም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው " - ኮሬ ዞን

🔵 " እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው " - የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ከትላንት በስቲያ ሁለት አርሶ አደሮች በታጣቂዎች ጥቃት እንደቆሰሉ ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ተወካይ አቶ አማረ አክሊሉ፣ ጉዳዩ በመንግስት ልዩ ትኩረት ስላልሰጠው አርሶ አደሮች በከፍተኛ ስጋት ላይ በመሆናቸው የፌዴራሉ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ጥቃቱን እንዲያስቆም ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አማረ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ትላንትም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው። አገዳደላቸው ራሱ ዘግናኝ ነው። 

አንድ ሰው ላይ እስከ 30 ጥይት ነው የሚያርከፈክፉት አጥንቱ እስኪታይ።

አሁን የመኸር እርሻ ወቅት በመሆኑ የአረም ሥራ ላይ ባሉ አርሶ አደሮች ነው ጥቃት እየደረሰ ያለው።

በአብዛኛው ጥቃቱ የሚሰነዘረው ጋላና ወረዳ ነው። ጥቃቱን የሚያደርሱት እዛው አካባቢ የመሸጉ ታጣቂዎች ናቸው።

ከምዕራብ ጉጂ ተነስተው ነው ጥቃት የሚፈጽሙት። በአካባቢው ላይ የመሬት ይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱ ናቸው።

በዋነናነት ‘ወደ 18 ቀበሌዎችን አፈናቅለን ቦታ ካልወሰድን’ የሚሉ አካላት ናቸው። በዚሁ ምክንያት ነው በአርሶ አደሮች ግድያና ድብደባ፣ በንብረት ላይ ዘረፋ እየተፈጸመ ያለው።

የፌደራል መንግስት ካልገባ የአካባቢው ችግር እየተወሳሰበ ነው። ጣልቃ ገብቶ ነጻ ካላወጣ በስተቀር ግድያው ከ6 ዓመታት በላይ አስቆጥሮም አልቆመም። የሸኔ ታጣቂ አለ፤ ጉጂ ላይ የተወሸቀ ሌላ ታጣቂም አለ
" ነው ያሉት። 

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮሬ ህዝብ ተወካይ ሀምዛዬ አወቀ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለቲክቫህ ሰጡት ቃል፣ " መንግስት ባለበት አገር ነው ህዝቡ ጥቃት የሚደርስበት። ጥቃት የሚደርስበትም ከኦሮሚያ ክልል ነው " ብለዋል።

" በቁጥሩ ትንሽ ስለሆነ ይሄ ህዝብ ብቻውን መጋፈጥ አይችልም። መንግስት መከታ ካልሆነው በስተቀር የህልውና አደጋ ውስጥ ነው። መንግስት ተገቢውን እርምጃ እየወሰደ አይደለም "  ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

ለችግሩ መፈጠር መሠረታዊ መንስዔው፤ ታጣቂዎች በግልጽ ከዛ ህዝብ የሚፈልጉት ጉዳይ ምንድን ነው ? ስንል ላቀረብለንላቸው ጥያቄ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" የችግሩ መሠረታዊ ነገር እውነት እንነጋገር ከተባለ የግዛት መስፋፋት ፍላጎት መኖር ነው። ምንም ሌላ ምክንያት የለውም። ‘ሸኔ’ ምናምን እየተባለ ሰበብ እየተደረገ ይቀርባል እንጂ።

እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው። በተለይ ከሁለት ቀበሌዎች ላይ ህዝቡ ከዚያ እንዲፈናቀል፤ እንዲጠፋ ተደርጓል።

ከዚያ በኋላ ግን እንደ አቡካዶ፣ ሙዝ የመሳሰሉ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ተነቅለው እንዲጠፉ፣ አካባቢው ወደ ባድማነት እንዲቀየር፣ ባዶ መሬት ነው ተብሎ እንዲሰጥ የተደረገበት ሁኔታ አለ። 

በ20ውም ቀበሌያት ወረራ ሲደረግ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ነው የሚነቀሉት። ይሄ የሚደረገው ለምንድን ነው? በሚል ብዙ ጊዜ እንጠይቃለን፤ የደረስንበትም ህዝቡን በማጥፋት መሬት ለመውረስ መሆኑን ነው
" ሲሉ አስረድተዋል።

ችግሩን ለምን ማስቆም እንዳልተቻለ ማብራሪያ እዲሰጡ በፅሑፍ መልዕክት ጭምር የጠየቅናቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ " የአመራር ስልጠና ላይ ነኝ " በማለት ዝርዝር ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😢260😭6966😡26🕊8🥰4👏4😱3



group-telegram.com/tikvahethiopia/91422
Create:
Last Update:

#ኮሬ

🛑 " ከትላንትና በስቲያም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው " - ኮሬ ዞን

🔵 " እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው " - የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ከትላንት በስቲያ ሁለት አርሶ አደሮች በታጣቂዎች ጥቃት እንደቆሰሉ ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ተወካይ አቶ አማረ አክሊሉ፣ ጉዳዩ በመንግስት ልዩ ትኩረት ስላልሰጠው አርሶ አደሮች በከፍተኛ ስጋት ላይ በመሆናቸው የፌዴራሉ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ጥቃቱን እንዲያስቆም ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አማረ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በጎርካ ወረዳ ዳኖ ቀበሌ ትላንትም ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ቆስለዋል። የአርሶ አደሩ ስጋት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው። አገዳደላቸው ራሱ ዘግናኝ ነው። 

አንድ ሰው ላይ እስከ 30 ጥይት ነው የሚያርከፈክፉት አጥንቱ እስኪታይ።

አሁን የመኸር እርሻ ወቅት በመሆኑ የአረም ሥራ ላይ ባሉ አርሶ አደሮች ነው ጥቃት እየደረሰ ያለው።

በአብዛኛው ጥቃቱ የሚሰነዘረው ጋላና ወረዳ ነው። ጥቃቱን የሚያደርሱት እዛው አካባቢ የመሸጉ ታጣቂዎች ናቸው።

ከምዕራብ ጉጂ ተነስተው ነው ጥቃት የሚፈጽሙት። በአካባቢው ላይ የመሬት ይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱ ናቸው።

በዋነናነት ‘ወደ 18 ቀበሌዎችን አፈናቅለን ቦታ ካልወሰድን’ የሚሉ አካላት ናቸው። በዚሁ ምክንያት ነው በአርሶ አደሮች ግድያና ድብደባ፣ በንብረት ላይ ዘረፋ እየተፈጸመ ያለው።

የፌደራል መንግስት ካልገባ የአካባቢው ችግር እየተወሳሰበ ነው። ጣልቃ ገብቶ ነጻ ካላወጣ በስተቀር ግድያው ከ6 ዓመታት በላይ አስቆጥሮም አልቆመም። የሸኔ ታጣቂ አለ፤ ጉጂ ላይ የተወሸቀ ሌላ ታጣቂም አለ
" ነው ያሉት። 

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮሬ ህዝብ ተወካይ ሀምዛዬ አወቀ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለቲክቫህ ሰጡት ቃል፣ " መንግስት ባለበት አገር ነው ህዝቡ ጥቃት የሚደርስበት። ጥቃት የሚደርስበትም ከኦሮሚያ ክልል ነው " ብለዋል።

" በቁጥሩ ትንሽ ስለሆነ ይሄ ህዝብ ብቻውን መጋፈጥ አይችልም። መንግስት መከታ ካልሆነው በስተቀር የህልውና አደጋ ውስጥ ነው። መንግስት ተገቢውን እርምጃ እየወሰደ አይደለም "  ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

ለችግሩ መፈጠር መሠረታዊ መንስዔው፤ ታጣቂዎች በግልጽ ከዛ ህዝብ የሚፈልጉት ጉዳይ ምንድን ነው ? ስንል ላቀረብለንላቸው ጥያቄ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" የችግሩ መሠረታዊ ነገር እውነት እንነጋገር ከተባለ የግዛት መስፋፋት ፍላጎት መኖር ነው። ምንም ሌላ ምክንያት የለውም። ‘ሸኔ’ ምናምን እየተባለ ሰበብ እየተደረገ ይቀርባል እንጂ።

እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ በማጽዳት መሬቱን መውሰድ ነው የተፈለገው። በተለይ ከሁለት ቀበሌዎች ላይ ህዝቡ ከዚያ እንዲፈናቀል፤ እንዲጠፋ ተደርጓል።

ከዚያ በኋላ ግን እንደ አቡካዶ፣ ሙዝ የመሳሰሉ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ተነቅለው እንዲጠፉ፣ አካባቢው ወደ ባድማነት እንዲቀየር፣ ባዶ መሬት ነው ተብሎ እንዲሰጥ የተደረገበት ሁኔታ አለ። 

በ20ውም ቀበሌያት ወረራ ሲደረግ ቋሚ ተክሎች ሁሉ ነው የሚነቀሉት። ይሄ የሚደረገው ለምንድን ነው? በሚል ብዙ ጊዜ እንጠይቃለን፤ የደረስንበትም ህዝቡን በማጥፋት መሬት ለመውረስ መሆኑን ነው
" ሲሉ አስረድተዋል።

ችግሩን ለምን ማስቆም እንዳልተቻለ ማብራሪያ እዲሰጡ በፅሑፍ መልዕክት ጭምር የጠየቅናቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ " የአመራር ስልጠና ላይ ነኝ " በማለት ዝርዝር ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/91422

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The perpetrators use various names to carry out the investment scams. They may also impersonate or clone licensed capital market intermediaries by using the names, logos, credentials, websites and other details of the legitimate entities to promote the illegal schemes. "Markets were cheering this economic recovery and return to strong economic growth, but the cheers will turn to tears if the inflation outbreak pushes businesses and consumers to the brink of recession," he added. Overall, extreme levels of fear in the market seems to have morphed into something more resembling concern. For example, the Cboe Volatility Index fell from its 2022 peak of 36, which it hit Monday, to around 30 on Friday, a sign of easing tensions. Meanwhile, while the price of WTI crude oil slipped from Sunday’s multiyear high $130 of barrel to $109 a pop. Markets have been expecting heavy restrictions on Russian oil, some of which the U.S. has already imposed, and that would reduce the global supply and bring about even more burdensome inflation. Recently, Durav wrote on his Telegram channel that users' right to privacy, in light of the war in Ukraine, is "sacred, now more than ever." Investors took profits on Friday while they could ahead of the weekend, explained Tom Essaye, founder of Sevens Report Research. Saturday and Sunday could easily bring unfortunate news on the war front—and traders would rather be able to sell any recent winnings at Friday’s earlier prices than wait for a potentially lower price at Monday’s open.
from it


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American