Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
" በትግራይ ያለው የፓለቲካ ሁኔታ ለድህንነቴ ያሰጋኛል ! " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ  የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዱባይ ይገኛሉ። በዱባይ ሆነውም ' bird story agency ' ለተባለ ሚድያ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል። ለህክምና በዱባይ እንደሚገኙና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ የገለፁት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው አስከ አሁን…
" ጊዜያዊ አስተዳደሩ በብዙ ውጣ ውረድ  ተቋቁሞ ፕሬዜዳንት ሆኜ መምራት ስጀምር በቀናት ውስጥ ' ባንዳ ' የሚል ስያሜ ተለጠፈብኝ " -  አቶ ጌታቸው ረዳ

ትላንት የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " UMD " ለተባለ ሚድያ ዘለግ ያለ ቃለመጠይቅ ሰጥተዋል።

በርካታ ጉዳዮች ባነሱበት ቃለ-መጠይቃቸው " አሁንም ትግራይ መላ ቅጡ በማይታወቅ ሁኔታ ላይ ናት ፤ በርካታ የትግራይ ህዝብ በከፍተኛ ጭንቅና መከራ ውስጥ ይገኛል " ብለዋል።

" በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ጊዚያዊ አስተዳደሩ ሲመሰረት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ጦርነቱ በመምራት ከፍተኛ ሚና የነበረን 5 ስራ አስፈፃሚዎች ወደ ፕሬዜዳንት የኋላፊነት ቦታ እንዳንመጣ ፍላጎት ነበረቸው " በማለት ወደ ኋላ ተመልሰው አስታውሰዋል።

ይህን ሃሳብ እሳቸው ቢቀበሉትም የተቀሩት አራቱ ስራ አስፈፃሚዎች የጠቅላይ ሚንስትሩን ሃሳብ ውድቅ ማድረጋቸው ተናግረዋል።

" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማቋቋም በአላስፈላጊ ክርክር አራት ወራት ፈጅተናል፤ በብዙ ውጣ ውረድ መጋቢት 21/2015 ዓ.ም ተቋቁሞ ፕሬዜዳንት ሆኜ መምራት ስጀምር በቀናት ውስጥ ' ባንዳ ' የሚል ስያሜ ተለጠፈብኝ " ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ጌታቸው " በዚያው ዓመት ወርሃ ግንቦት የባሰውኑ ' ከሃዲ ' ተባልኩኝ " በማለት ተናግረዋል።

" አራቱ የህወሓት ስራ አስፈፃሚዎች በየሦስት ወሩ ለማድረግ የሚፈቅደውን የድርጅቱ ውስጠ ደንብ በመጣስ በየሦስት ቀኑ ፍሬ በሌለው ስብሰባ በመጥመድ ከመንግስታዊ ስራ ውጭ እንድሆን አበክረው ሰርተዋል ፤ በዚሁ ተማርሬ ኃላፊነቴ በራሴ ፍቃድ መልቀቅ ባለመቻሌ ተናደው እኔን ጨምሮ 16 የድርጅቱ ማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን ' ከሃዲዎች ከጂዎች ' ብለው በመፈረጅ አላሰራ አሉን " ብለዋል።

" የተቀረው የህወሓት የስራ አስፈፃሚ በፕሪቶሪያው የተኩስ ማቆም ስምምነት እንደ ሽንፈት የሚቆጥር ፣ በተፈናቃዮች እጣ ፈንታ የሚቆምር ፣ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጡት ተልእኮዎች እንዳይፈፅም ከላይ እስከ ታች በእቅድ የሰራ አደናቃፊ " ብለውታል አቶ ጌታቸው።

አቶ ጌታቸው " ለውጥ የማይቀበሉ ፤ የተቸከሉ " ሲሉ የገለፁዋቸው የህወሓት 4ቱ ስራ አስፈፃሚዎች እሳቸው ወደ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት በመጡበት ማግስት የሚሰራ በሌለበት 55 የድርጅቱ ሰዎች በምክትል የስራ ኃላፊ ደረጃ እንዲሾሙ ፕሮፓዛል እንዳቀረቡላቸው ፤ ይህንን ያህል ቁጥር ያለው ስራ ሳይሰራ ደመወዝ የሚከፈለው አመራር ለመመደብ ቢቸገሩም ከክርክር በኋላ 35
#በግድ መመደባቸው ገልጸዋል።

ድርጅታዊ ውስጥ ደንብ በመጣስ የ65 እና የ70 ዓመት ዕድሜ ያላቸው የማእከላይ ኮሚቴ አመራር እንዲሆኑ መመረጣቸው በርካታ ቁጥር ያለው አመራር ከሃላፊነት ምድብ ውጭ ሆኖም ቁጭ ብሎ በፊት የነበረው ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም እንዲያገኝ የሚያደርግ እጅግ ዘግናኝ አሰራር ክልሉን ጠልፎ መጣሉ አቶ ጌታቸው ገልፀዋል።

" ጡረታ የማይፈቀድበት ክልል ቢኖር ትግራይ ነው "  ያሉት አቶ ጌታቸው  ፤ ከጦርነቱ በፊት በ2012 ዓ.ም 800 ሚሊዮን ብር የነበረው የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ተቋቁሞ ስራው በ2015 ዓ.ም ሲጀምር ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ማሻቀቡ በክልሉ ያለው ቅጥ ያጣ በልሹ አሰራር የሚያሳይ ነው ብለዋል።

" በትግራይ ያለው አሁናዊ ፓለቲካዊ ቀውስና ችግር ህወሓት ብቻውን ስልጣን እንዲቆጣጠር ያለው ያልተገራ ፍላጎት የፈጠረው ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " ይህንን ሁሉንም ነገር በብቸኝነት የመያዝ ያልተገራ የህወሓት ፍላጎት የማይሸከም በተግባር የተደገፈ ለውጥ በትግራይ መፈጠሩ ማሳያዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል።

ከትናንት ወዲህ መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም ከዱባይ ' bird story agency ' ለተባለ ሚድያ በሰጡት ቃለመጠይቅ " በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እመለሳሎህ ማለታቸው " ተከትሎ ትናንት ወደ አዲሰ አበባ መመለሳቸው በአንዳንድ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች ቢፃፍም ፤ ፕሬዜዳንቱ ለUMD ሚድያ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ ስለዚሁ ጉዳይ ያሉት የለም።

NB. አቶ ጌታቸው ረዳ አራቱ ስራ አስፈጻሚዎች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ ውድቅ እንዳደረጉ በገለጹበት አውድ ስም ባይጠቅሱም በይፋ የሚታወቁት ስራ አስፈጻሚዎች ፦
1. ደብረፅዮን (ዶ/ር)
2. ወ/ሮ ፈትለወርቅ
3. አቶ ኣለም ገብረዋህድ
4. አቶ ጌታቸው ኣሰፋ ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
524🕊132🤔86😭53😡51🙏38🥰22👏17😱17😢7💔7



group-telegram.com/tikvahethiopia/95661
Create:
Last Update:

" ጊዜያዊ አስተዳደሩ በብዙ ውጣ ውረድ  ተቋቁሞ ፕሬዜዳንት ሆኜ መምራት ስጀምር በቀናት ውስጥ ' ባንዳ ' የሚል ስያሜ ተለጠፈብኝ " -  አቶ ጌታቸው ረዳ

ትላንት የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " UMD " ለተባለ ሚድያ ዘለግ ያለ ቃለመጠይቅ ሰጥተዋል።

በርካታ ጉዳዮች ባነሱበት ቃለ-መጠይቃቸው " አሁንም ትግራይ መላ ቅጡ በማይታወቅ ሁኔታ ላይ ናት ፤ በርካታ የትግራይ ህዝብ በከፍተኛ ጭንቅና መከራ ውስጥ ይገኛል " ብለዋል።

" በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ጊዚያዊ አስተዳደሩ ሲመሰረት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ጦርነቱ በመምራት ከፍተኛ ሚና የነበረን 5 ስራ አስፈፃሚዎች ወደ ፕሬዜዳንት የኋላፊነት ቦታ እንዳንመጣ ፍላጎት ነበረቸው " በማለት ወደ ኋላ ተመልሰው አስታውሰዋል።

ይህን ሃሳብ እሳቸው ቢቀበሉትም የተቀሩት አራቱ ስራ አስፈፃሚዎች የጠቅላይ ሚንስትሩን ሃሳብ ውድቅ ማድረጋቸው ተናግረዋል።

" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማቋቋም በአላስፈላጊ ክርክር አራት ወራት ፈጅተናል፤ በብዙ ውጣ ውረድ መጋቢት 21/2015 ዓ.ም ተቋቁሞ ፕሬዜዳንት ሆኜ መምራት ስጀምር በቀናት ውስጥ ' ባንዳ ' የሚል ስያሜ ተለጠፈብኝ " ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ጌታቸው " በዚያው ዓመት ወርሃ ግንቦት የባሰውኑ ' ከሃዲ ' ተባልኩኝ " በማለት ተናግረዋል።

" አራቱ የህወሓት ስራ አስፈፃሚዎች በየሦስት ወሩ ለማድረግ የሚፈቅደውን የድርጅቱ ውስጠ ደንብ በመጣስ በየሦስት ቀኑ ፍሬ በሌለው ስብሰባ በመጥመድ ከመንግስታዊ ስራ ውጭ እንድሆን አበክረው ሰርተዋል ፤ በዚሁ ተማርሬ ኃላፊነቴ በራሴ ፍቃድ መልቀቅ ባለመቻሌ ተናደው እኔን ጨምሮ 16 የድርጅቱ ማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን ' ከሃዲዎች ከጂዎች ' ብለው በመፈረጅ አላሰራ አሉን " ብለዋል።

" የተቀረው የህወሓት የስራ አስፈፃሚ በፕሪቶሪያው የተኩስ ማቆም ስምምነት እንደ ሽንፈት የሚቆጥር ፣ በተፈናቃዮች እጣ ፈንታ የሚቆምር ፣ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጡት ተልእኮዎች እንዳይፈፅም ከላይ እስከ ታች በእቅድ የሰራ አደናቃፊ " ብለውታል አቶ ጌታቸው።

አቶ ጌታቸው " ለውጥ የማይቀበሉ ፤ የተቸከሉ " ሲሉ የገለፁዋቸው የህወሓት 4ቱ ስራ አስፈፃሚዎች እሳቸው ወደ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት በመጡበት ማግስት የሚሰራ በሌለበት 55 የድርጅቱ ሰዎች በምክትል የስራ ኃላፊ ደረጃ እንዲሾሙ ፕሮፓዛል እንዳቀረቡላቸው ፤ ይህንን ያህል ቁጥር ያለው ስራ ሳይሰራ ደመወዝ የሚከፈለው አመራር ለመመደብ ቢቸገሩም ከክርክር በኋላ 35
#በግድ መመደባቸው ገልጸዋል።

ድርጅታዊ ውስጥ ደንብ በመጣስ የ65 እና የ70 ዓመት ዕድሜ ያላቸው የማእከላይ ኮሚቴ አመራር እንዲሆኑ መመረጣቸው በርካታ ቁጥር ያለው አመራር ከሃላፊነት ምድብ ውጭ ሆኖም ቁጭ ብሎ በፊት የነበረው ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም እንዲያገኝ የሚያደርግ እጅግ ዘግናኝ አሰራር ክልሉን ጠልፎ መጣሉ አቶ ጌታቸው ገልፀዋል።

" ጡረታ የማይፈቀድበት ክልል ቢኖር ትግራይ ነው "  ያሉት አቶ ጌታቸው  ፤ ከጦርነቱ በፊት በ2012 ዓ.ም 800 ሚሊዮን ብር የነበረው የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ተቋቁሞ ስራው በ2015 ዓ.ም ሲጀምር ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ማሻቀቡ በክልሉ ያለው ቅጥ ያጣ በልሹ አሰራር የሚያሳይ ነው ብለዋል።

" በትግራይ ያለው አሁናዊ ፓለቲካዊ ቀውስና ችግር ህወሓት ብቻውን ስልጣን እንዲቆጣጠር ያለው ያልተገራ ፍላጎት የፈጠረው ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " ይህንን ሁሉንም ነገር በብቸኝነት የመያዝ ያልተገራ የህወሓት ፍላጎት የማይሸከም በተግባር የተደገፈ ለውጥ በትግራይ መፈጠሩ ማሳያዎችን በመጥቀስ አስረድተዋል።

ከትናንት ወዲህ መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም ከዱባይ ' bird story agency ' ለተባለ ሚድያ በሰጡት ቃለመጠይቅ " በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እመለሳሎህ ማለታቸው " ተከትሎ ትናንት ወደ አዲሰ አበባ መመለሳቸው በአንዳንድ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች ቢፃፍም ፤ ፕሬዜዳንቱ ለUMD ሚድያ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ ስለዚሁ ጉዳይ ያሉት የለም።

NB. አቶ ጌታቸው ረዳ አራቱ ስራ አስፈጻሚዎች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ ውድቅ እንዳደረጉ በገለጹበት አውድ ስም ባይጠቅሱም በይፋ የሚታወቁት ስራ አስፈጻሚዎች ፦
1. ደብረፅዮን (ዶ/ር)
2. ወ/ሮ ፈትለወርቅ
3. አቶ ኣለም ገብረዋህድ
4. አቶ ጌታቸው ኣሰፋ ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/95661

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

"And that set off kind of a battle royale for control of the platform that Durov eventually lost," said Nathalie Maréchal of the Washington advocacy group Ranking Digital Rights. Telegram, which does little policing of its content, has also became a hub for Russian propaganda and misinformation. Many pro-Kremlin channels have become popular, alongside accounts of journalists and other independent observers. WhatsApp, a rival messaging platform, introduced some measures to counter disinformation when Covid-19 was first sweeping the world. For tech stocks, “the main thing is yields,” Essaye said. In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback.
from it


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American