Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ ነው " - የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ

የህዝቡ ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦችላይ  የማያዳግም አርምጃ እንደሚወሰድ የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ በጥብቅ አስጠነቀቀ።

ቢሮው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14
/2017 ዓ.ም ያወጡትን መግለጫ ተከትሎ " የማያሻማ የመግለጫውን ትርጉም ወደ ጎን በመተው ለራሳቸው የፓለቲካ ማራመጃ በማለም  ጉዳዩን እያወሳሰቡት ይገኛሉ ብሏል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14 / 2017 ዓ.ም ያወጡት መግለጫ የድጋፍ እና ተቃውሞ ሰልፍ የሚያስፈልገው እንዳልሆነ የጠቀሰው ቢሮው " መግለጫውን የተለያዩ ትርጉሞች በመሰጠት ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ እየተመለከትን ነው " ሲል ገልጿል።

በተለያዩ አደረጃጀቶች ስም ተሸፍኖ በአንዳንድ ግለሰቦች እየተሰጠ እና እየተሰራጨ ያለውንና  " የበላይ ወታደራዊ  ኃይል አመራሮች " የሰጡት መግለጫ አቋም የማይወክሉ መልእክቶች በአስቸኳይ መታረም አለባቸው ብለዋል ቢሮው።

በተሳሳቱ ቅስቀሳዎች ህዝቡን ወደ ሁከት እና ብጥብጥ የሚመሩ ብሎም ስርአት አለበኝነት እንዲነገስ የሚሯሯጡ አካላት ወደ ቀልባቸው እንዲመለሱ እና ከማንኛውም ህገ-ወጥ ተግባር እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

" ያለውን ሁኔታ የሌለውን መልክ በማስያዝ ፦
- ሰልፍ ማደራጀት ፣
- የመንግስት አገልግሎት ማስተጓጎል እና ማቋረጥ ፣
- መንገድ በመዝጋት እንቅስቃሴ ማወክ እና ማደናቀፍ፣
- ሃይል በመጠቀም የግል ፍላጎት ለማሳካት የሚደረግ እንቅስቃሴ ፍፁም የማይፈቅድ መሆኑ አጥብቆ አሳስቧል።

ህዝቡ ከዚህ መሰል ተግባር እንዲርቅ ወደ ህገ-ወጥ ተግባሩ የሚቀላቀሉ እንዲመክር እና እንዲገስፅ ፤ምክር እና ተግሳፁን በመጣስ ወደ ሁከት እና ግርግር የሚገቡት ደግሞ እንዲኮንን ጥሪ አቅርቧል።

ቢሮው የሚያቀርበው ምክር እና መረጃ ወደ ጎን በመተው በድጋፍ እና ተቃውሞ ስም ወደ ጥፍት በሚገቡትንና በአስተባባሪዎቻቸው ላይ ስርአት የማስከበር ስራ ይሰራል ብሏል።

የህዝቡን ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።


@tikvahethiopia
🕊20592🙏50😡39👏14🤔14😱13😭13🥰5😢5



group-telegram.com/tikvahethiopia/94037
Create:
Last Update:

" ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ ነው " - የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ

የህዝቡ ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦችላይ  የማያዳግም አርምጃ እንደሚወሰድ የትግራይ የሰላም እና የፀጥታ ቢሮ በጥብቅ አስጠነቀቀ።

ቢሮው " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14
/2017 ዓ.ም ያወጡትን መግለጫ ተከትሎ " የማያሻማ የመግለጫውን ትርጉም ወደ ጎን በመተው ለራሳቸው የፓለቲካ ማራመጃ በማለም  ጉዳዩን እያወሳሰቡት ይገኛሉ ብሏል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች " ጥር 14 / 2017 ዓ.ም ያወጡት መግለጫ የድጋፍ እና ተቃውሞ ሰልፍ የሚያስፈልገው እንዳልሆነ የጠቀሰው ቢሮው " መግለጫውን የተለያዩ ትርጉሞች በመሰጠት ወደ ግርግር እና ረብሻ የሚመሩ የተዛቡ ሁከት ቀስቃሽ መልዕክቶች እየተሰራጩ እየተመለከትን ነው " ሲል ገልጿል።

በተለያዩ አደረጃጀቶች ስም ተሸፍኖ በአንዳንድ ግለሰቦች እየተሰጠ እና እየተሰራጨ ያለውንና  " የበላይ ወታደራዊ  ኃይል አመራሮች " የሰጡት መግለጫ አቋም የማይወክሉ መልእክቶች በአስቸኳይ መታረም አለባቸው ብለዋል ቢሮው።

በተሳሳቱ ቅስቀሳዎች ህዝቡን ወደ ሁከት እና ብጥብጥ የሚመሩ ብሎም ስርአት አለበኝነት እንዲነገስ የሚሯሯጡ አካላት ወደ ቀልባቸው እንዲመለሱ እና ከማንኛውም ህገ-ወጥ ተግባር እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

" ያለውን ሁኔታ የሌለውን መልክ በማስያዝ ፦
- ሰልፍ ማደራጀት ፣
- የመንግስት አገልግሎት ማስተጓጎል እና ማቋረጥ ፣
- መንገድ በመዝጋት እንቅስቃሴ ማወክ እና ማደናቀፍ፣
- ሃይል በመጠቀም የግል ፍላጎት ለማሳካት የሚደረግ እንቅስቃሴ ፍፁም የማይፈቅድ መሆኑ አጥብቆ አሳስቧል።

ህዝቡ ከዚህ መሰል ተግባር እንዲርቅ ወደ ህገ-ወጥ ተግባሩ የሚቀላቀሉ እንዲመክር እና እንዲገስፅ ፤ምክር እና ተግሳፁን በመጣስ ወደ ሁከት እና ግርግር የሚገቡት ደግሞ እንዲኮንን ጥሪ አቅርቧል።

ቢሮው የሚያቀርበው ምክር እና መረጃ ወደ ጎን በመተው በድጋፍ እና ተቃውሞ ስም ወደ ጥፍት በሚገቡትንና በአስተባባሪዎቻቸው ላይ ስርአት የማስከበር ስራ ይሰራል ብሏል።

የህዝቡን ሰላም እና ፀጥታ በሚያውኩ አካላትም ይሁን ግለሰቦች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።


@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94037

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War." The regulator said it has been undertaking several campaigns to educate the investors to be vigilant while taking investment decisions based on stock tips. The Securities and Exchange Board of India (Sebi) had carried out a similar exercise in 2017 in a matter related to circulation of messages through WhatsApp. The message was not authentic, with the real Zelenskiy soon denying the claim on his official Telegram channel, but the incident highlighted a major problem: disinformation quickly spreads unchecked on the encrypted app. Meanwhile, a completely redesigned attachment menu appears when sending multiple photos or vides. Users can tap "X selected" (X being the number of items) at the top of the panel to preview how the album will look in the chat when it's sent, as well as rearrange or remove selected media.
from kr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American