Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

የ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች ፥ " ለ20 ዓመታት ቤት ይደርሰናል ብለን ስንጠብቅ ከሰሞኑን የሰማነው ነገር አሳዝኖናል ፤ ፍትህ ተጓድሎብናል መፍትሄ እንፈልጋለን ፤ በቤት ኪራይ ተሰቃየን ፤ የቤት ችግር ኑሯችንን ፈተና ላይ ጥሎታል " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

ትላንት ምሽት የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ማብራሪያ መስጠቱ ይታወሳል።

ዛሬ ደግሞ አስተዳደሩ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ማብራሪያ ሰጥቷል።

ኮርፖሬሽኑ ምን አለ ?

" ብቁና ንቁ የነበሩ የ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች በ14ኛው ዙር ዕጣ ሙሉ በሙሉ ተስተናግደዋል " ብሏል።

" በ1997 ዓ/ም የቤት ባለቤት ለመሆን ተመዝግበው የነበሩ የከተማችን ነዋሪዎች በ2005 ዓ.ም በተካሄደው ዳግም ምዝገባ ወቅት ' ነባር ' የሚል መለያ ተሰጥቷቸው የነበረ ሲሆን ዳግም ከተመዘገቡና ውላቸውን ካደሱ ጊዜ ጀምሮ ሳያቋርጡ ሲቆጥቡ የነበሩ ናቸው " ሲል ገልጿል።  

" እነዚህ ተመዝጋቢዎች ቀደም ብለው የተመዘገቡ እንደመሆናቸው መጠን በ20/80 የቤት ልማት መርሃ ግብር ተገንብተው ለእጣ ከሚተላለፉት ቤቶች ውስጥ የጋራ መኖሪያና ንግድ ቤቶች ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ በወጣው መመርያ ቁጥር 3/2011 መሰረት በነበሩት ዙሮች ቅድሚያ እየተሰጣቸው ሙሉ በሙሉ ተስተናግደዋል " ሲል አሳውቋል።

" በ2005 ዳግም ምዝገባ ያደረጉ ከ140 ሺህ በላይ ተመዝጋቢዎች ሳያቆራርጡ እስከ እጣ ማውጫ ቀን ድረስ እየቆጠቡ ለነበሩት እስከ 13ኛ ዙር በነበረው የጋራ መኖርያ ቤቶች እጣ ሲሰተናገዱ ቆይተዋል " ብሏል።

" ህዳር 6 ቀን 2015 ዓ.ም ለ14ኛ ዙር በተላለፉት የ20/80 የጋራ መኖርያ ቤቶች ላይም የ1997 ተመዝጋቢዎች ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ነው የተስተናገዱት " ሲል አብራርቷል።

" በ14ኛ ዙር እጣ ዝግጅት በሚደረግበት ወቅት ንቁና ብቁ የነበሩ ከ43 ሺህ ያልበለጡ ቆጣቢዎች ቅድሚያ በመስጠት ሙሉ በሙሉ እንዲሰተናገዱ ተደርጓል " ነው ያለው።

" በእጣ ማውጫ ጊዜ በመረጃ ቋት ውስጥ የቀሩት የ1997 ተመዝጋቢዎች በጊዜው ንቁና ብቁ ያልነበሩ ናቸው "ብሏል።

" እነዚህና ሌሎች ቤት ፈላጊዎች በከተማ አስተዳደሩ እየተተገበሩ በሚገኙ የተለያዩ የቤት የልማት አማራጮች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛሉ " ሲልም አመልክቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ፥ " በአሁኑ ወቅት በከተማዋ እየተካሄዱ በሚገኙ የልማት ስራዎች ምክንያት ከመኖርያ አካባቢያቸው ለሚነሱ የልማት ተነሽዎች በአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የወጣው በጋራ መኖሪያና ንግድ ቤቶች ማስተላለፍ መመርያ ቁጥር 3/2011 አንቀጽ 23 በተገለጸው መሰረት በከተማ መልሶ ማልማት ምክንያት ለሚነሱ ነዋሪዎች ምትክ ቤት ለመመደብ በተቀመጠው አሰራር መሰረት እየተስተናገዱ ናቸው " ብሏል።

ኤጀንሲው " በልማት ምክንያት የሚነሱ ነዋሪዎች ምትክ ቤት የሚሰጣቸው ከላይ በተጠቀሰው መመርያ ላይ በሰፈረው መሰረት በከተማ አስተዳደሩ ከሚገነቡ የጋራ መኖርያ ቤቶች ውስጥ ለልማት ተነሺ በሚል በመጠባበቂያ ከተያዙት ቤቶች እንጂ በመደበኛነት ለተመዝጋቢዎች ከሚተላለፉ ቤቶች አይደለም " ብሏል።

" የልማት ተነሺ ሆነው የጋራ መኖርያ ቤት ምትክ የወሰዱና በ20/80 ወይም በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራሞች ተመዝጋቢ የሆኑ ነዋሪዎች ከምዝገባ ቋት ውስጥ የሚቀነሱ ይሆናል " ሲልም አመልክቷል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
😱204130😡102😭68🤔22😢16🥰12🙏10🕊9👏3



group-telegram.com/tikvahethiopia/91737
Create:
Last Update:

#AddisAbaba

የ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች ፥ " ለ20 ዓመታት ቤት ይደርሰናል ብለን ስንጠብቅ ከሰሞኑን የሰማነው ነገር አሳዝኖናል ፤ ፍትህ ተጓድሎብናል መፍትሄ እንፈልጋለን ፤ በቤት ኪራይ ተሰቃየን ፤ የቤት ችግር ኑሯችንን ፈተና ላይ ጥሎታል " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

ትላንት ምሽት የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ማብራሪያ መስጠቱ ይታወሳል።

ዛሬ ደግሞ አስተዳደሩ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በኩል ማብራሪያ ሰጥቷል።

ኮርፖሬሽኑ ምን አለ ?

" ብቁና ንቁ የነበሩ የ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች በ14ኛው ዙር ዕጣ ሙሉ በሙሉ ተስተናግደዋል " ብሏል።

" በ1997 ዓ/ም የቤት ባለቤት ለመሆን ተመዝግበው የነበሩ የከተማችን ነዋሪዎች በ2005 ዓ.ም በተካሄደው ዳግም ምዝገባ ወቅት ' ነባር ' የሚል መለያ ተሰጥቷቸው የነበረ ሲሆን ዳግም ከተመዘገቡና ውላቸውን ካደሱ ጊዜ ጀምሮ ሳያቋርጡ ሲቆጥቡ የነበሩ ናቸው " ሲል ገልጿል።  

" እነዚህ ተመዝጋቢዎች ቀደም ብለው የተመዘገቡ እንደመሆናቸው መጠን በ20/80 የቤት ልማት መርሃ ግብር ተገንብተው ለእጣ ከሚተላለፉት ቤቶች ውስጥ የጋራ መኖሪያና ንግድ ቤቶች ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ በወጣው መመርያ ቁጥር 3/2011 መሰረት በነበሩት ዙሮች ቅድሚያ እየተሰጣቸው ሙሉ በሙሉ ተስተናግደዋል " ሲል አሳውቋል።

" በ2005 ዳግም ምዝገባ ያደረጉ ከ140 ሺህ በላይ ተመዝጋቢዎች ሳያቆራርጡ እስከ እጣ ማውጫ ቀን ድረስ እየቆጠቡ ለነበሩት እስከ 13ኛ ዙር በነበረው የጋራ መኖርያ ቤቶች እጣ ሲሰተናገዱ ቆይተዋል " ብሏል።

" ህዳር 6 ቀን 2015 ዓ.ም ለ14ኛ ዙር በተላለፉት የ20/80 የጋራ መኖርያ ቤቶች ላይም የ1997 ተመዝጋቢዎች ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ነው የተስተናገዱት " ሲል አብራርቷል።

" በ14ኛ ዙር እጣ ዝግጅት በሚደረግበት ወቅት ንቁና ብቁ የነበሩ ከ43 ሺህ ያልበለጡ ቆጣቢዎች ቅድሚያ በመስጠት ሙሉ በሙሉ እንዲሰተናገዱ ተደርጓል " ነው ያለው።

" በእጣ ማውጫ ጊዜ በመረጃ ቋት ውስጥ የቀሩት የ1997 ተመዝጋቢዎች በጊዜው ንቁና ብቁ ያልነበሩ ናቸው "ብሏል።

" እነዚህና ሌሎች ቤት ፈላጊዎች በከተማ አስተዳደሩ እየተተገበሩ በሚገኙ የተለያዩ የቤት የልማት አማራጮች ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛሉ " ሲልም አመልክቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ፥ " በአሁኑ ወቅት በከተማዋ እየተካሄዱ በሚገኙ የልማት ስራዎች ምክንያት ከመኖርያ አካባቢያቸው ለሚነሱ የልማት ተነሽዎች በአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የወጣው በጋራ መኖሪያና ንግድ ቤቶች ማስተላለፍ መመርያ ቁጥር 3/2011 አንቀጽ 23 በተገለጸው መሰረት በከተማ መልሶ ማልማት ምክንያት ለሚነሱ ነዋሪዎች ምትክ ቤት ለመመደብ በተቀመጠው አሰራር መሰረት እየተስተናገዱ ናቸው " ብሏል።

ኤጀንሲው " በልማት ምክንያት የሚነሱ ነዋሪዎች ምትክ ቤት የሚሰጣቸው ከላይ በተጠቀሰው መመርያ ላይ በሰፈረው መሰረት በከተማ አስተዳደሩ ከሚገነቡ የጋራ መኖርያ ቤቶች ውስጥ ለልማት ተነሺ በሚል በመጠባበቂያ ከተያዙት ቤቶች እንጂ በመደበኛነት ለተመዝጋቢዎች ከሚተላለፉ ቤቶች አይደለም " ብሏል።

" የልማት ተነሺ ሆነው የጋራ መኖርያ ቤት ምትክ የወሰዱና በ20/80 ወይም በ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራሞች ተመዝጋቢ የሆኑ ነዋሪዎች ከምዝገባ ቋት ውስጥ የሚቀነሱ ይሆናል " ሲልም አመልክቷል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/91737

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

At this point, however, Durov had already been working on Telegram with his brother, and further planned a mobile-first social network with an explicit focus on anti-censorship. Later in April, he told TechCrunch that he had left Russia and had “no plans to go back,” saying that the nation was currently “incompatible with internet business at the moment.” He added later that he was looking for a country that matched his libertarian ideals to base his next startup. Official government accounts have also spread fake fact checks. An official Twitter account for the Russia diplomatic mission in Geneva shared a fake debunking video claiming without evidence that "Western and Ukrainian media are creating thousands of fake news on Russia every day." The video, which has amassed almost 30,000 views, offered a "how-to" spot misinformation. Pavel Durov, a billionaire who embraces an all-black wardrobe and is often compared to the character Neo from "the Matrix," funds Telegram through his personal wealth and debt financing. And despite being one of the world's most popular tech companies, Telegram reportedly has only about 30 employees who defer to Durov for most major decisions about the platform. Markets continued to grapple with the economic and corporate earnings implications relating to the Russia-Ukraine conflict. “We have a ton of uncertainty right now,” said Stephanie Link, chief investment strategist and portfolio manager at Hightower Advisors. “We’re dealing with a war, we’re dealing with inflation. We don’t know what it means to earnings.” NEWS
from ms


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American