Telegram Group & Telegram Channel
" የሀገር ሀብትና የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉ የቡና ምርት በቀልጣፋ አገልግሎት እጦት ለጥራት ችግር እየተዳረገብን ነዉ " - የቡና አቅራቢዎች

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርመራና ሰርትፊኬሽን ማዕከል በሀገራች ከፍተኛ ቡና አምራች ከሚባሉ ሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ ሻኪሶ ፣ ቡሌሆራ እና አማሮ አከባቢዎች የሚገኙ ምርቶች የጥራት ልኬት እና ሰርትፊኬሽን አግኝተዉ ቡናን ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚቀርቡበት ማዕከል ነው።

በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሀዋሳ ከተማ ተቋሙ ከሚገኝበት የቀድሞዉ የደቡብ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ግቢ ዙሪያ በአራቱም አቅጣጫ ቡና የጫኑ በርካታ ተሸከርካሪዎችን ማየት የተለመደ ሆኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምክንያቱን ለማጣራት ክትትል አድርጓል።

የቡና አቅራቢዎች እና አሽከርካሪዎችን ያነጋገርን ሲሆን ፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተቋሙ ባለዉ የወረፋ ብዛትና ተያያዥ ችግሮች ላላስፈላጊ ወጪ መዳረጋቸዉንና አልፎም ለሀገር ትልቅ የገቢ ምንጭ በሆነዉ የቡና ምርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል።

" ቡና በባህሪው እንደ ሙሽራ እንክብካቤ ይፈልጋል " ያሉን አንድ የቡና ላኪ " በቦታዉ ባለዉ ወረፋ መብዛትና ተገቢነት በለሌዉ የተሽከርካሪ አቋቋም ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረግን ነዉ " ብለዋል።

" በማዕከሉ ዙሪያ ተሰልፈን አምስትና ስድስት ቀናትና አለፍ ሲልም ከዛም በላይ አስር ቀን የመቆየት ሁኔታዎች አሉ " ያሉን ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ የቡና አቅራቢ " ቡና ሳይወጋ በሻራ ዉስጥ ታፍኖ ለረጅም ቀናት ስለሚቆይ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በሚናቀርብበት ወቅት የጥራት ደረጃ መዉረድና በከፍተኛ ሁኔታ የኪሎግራም መቀነስ እያጋጠመን ነዉ " ብለዋል።

" ቀልጣፋ አገልግሎት ባለማግኘታችን በእኛና በተሽከርካሪ ባለቤቶች እንዲሁም በቡና አቅራቢዎች እና ጉዳይ አስፈፃሚዎች መካከል አለመተማመኖች እየተፈጠሩ ነዉ " ያሉን አሽከርካሪዎች " ለፓርኪንግ፣ ምግብ ፣ አልጋ መሰል አላስፈላጊ ወጪዎችን እያወጣን ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ቡና በሀገር ደረጃ ባለዉ ከፍተኛ የገቢ ምንጭነት ልክ ትኩረት አልተሰጠውም " የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ " ፈጣን መፍትሔ ካልተበጀለት ጉዳቱ ከኛ አልፎ አምራች አርሶአደሮች፣ ሰፊ የስራ ዕድል በተፈጠረላቸው ወጣቶችና በሀገር የዉጪ ምንዛሪ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ማሳደሩ አይቀርም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ስሜን አነጋግሯል።

እሳቸውም ፤ የዘንድሮ የቡና ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ቀደም ሲል ከነበረዉ የቦታ ጥበትና ተያያዥ ችግሮች ጋር ተዳምሮ ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ አለመሆን ዋነኛ ምክንያት መሆናቸዉን ተናግረዋል።

የችግሩን አሳሳብነትና የቡናን ሀገራዊ ጥቅሙን በመግለፅ ለሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ደብዳቤ መፃፋቸዉንና ምላሽም እየተጠባበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ መልኩ የቡና ምርቶች ወደ ማዕከሉ በሚደርሱበት ወቅት አስፈላጊዉ የእርጥበት መጠን ላይ ሳይደርሱ የሚመጡበት አጋጣሚዎች ስላሉ ተገቢዉ የእርጥበት መጠናቸዉ ላይ እስኪደርሱ ድረስ መወጋትም ሆነ የቅምሻ ልኬት ስለማይደረግላቸዉና ለኮንትሮባንድ እንዳይጋለጡ ሲባል ወደ ኋላ ስለማይመለሱ በማዕከሉ እንዲቆዩ ስለሚደረግ የተሽከርካሪዎች ክምችት እንደሚፋጠርም አስታውቀዋል።

ማዕከሉ ለሲዳማ፣ ለደቡብ ኢትዮጵያና ኦሮሚያ ክልል ቡና አምራች አከባቢዎች አገልግሎት የሚሰጥና የሀገራችንን ዋነኛ የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የሚያቀርብ እንደመሆኑ መጠን በተለይም የሲዳማ ክልል መንግስትና ተጠሪ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ መፍትሔ ቢሰጡ ጥሩ ነው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬን አነጋግሯል።

" ቡና ለሲዳማ ክልል ልዩ ትርጉም ያለዉ የገቢ ምንጭና የክልሉም መለያም ጭምር ነዉ " ያሉ ሲሆን በ2017 ዓ/ም ብቻ ከክልሉ ከ37 ሺ ቶን በላይ ቡና መሰብሰቡን ገልፀዉ በዘንድሮዉ ሀገር አቀፍ የቡና ቅምሻ ወድድር (ካፕ ኦፍ ኤክሰሌንስ) ከ1ኛ እስከ 39ኛ ድረስ የወጡት የክልሉ አምራች አርሶ አደሮች መሆናቸውን አስታዉቀዋል።

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ያለበትን ጫና የክልሉ መንግስት መረዳቱንና በአጭር ጊዜ ዉስጥ አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
293😡58😭36🙏30🕊21🤔15😱12🥰11😢9👏1



group-telegram.com/tikvahethiopia/93774
Create:
Last Update:

" የሀገር ሀብትና የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉ የቡና ምርት በቀልጣፋ አገልግሎት እጦት ለጥራት ችግር እየተዳረገብን ነዉ " - የቡና አቅራቢዎች

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርመራና ሰርትፊኬሽን ማዕከል በሀገራች ከፍተኛ ቡና አምራች ከሚባሉ ሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ ሻኪሶ ፣ ቡሌሆራ እና አማሮ አከባቢዎች የሚገኙ ምርቶች የጥራት ልኬት እና ሰርትፊኬሽን አግኝተዉ ቡናን ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚቀርቡበት ማዕከል ነው።

በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሀዋሳ ከተማ ተቋሙ ከሚገኝበት የቀድሞዉ የደቡብ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ግቢ ዙሪያ በአራቱም አቅጣጫ ቡና የጫኑ በርካታ ተሸከርካሪዎችን ማየት የተለመደ ሆኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምክንያቱን ለማጣራት ክትትል አድርጓል።

የቡና አቅራቢዎች እና አሽከርካሪዎችን ያነጋገርን ሲሆን ፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተቋሙ ባለዉ የወረፋ ብዛትና ተያያዥ ችግሮች ላላስፈላጊ ወጪ መዳረጋቸዉንና አልፎም ለሀገር ትልቅ የገቢ ምንጭ በሆነዉ የቡና ምርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል።

" ቡና በባህሪው እንደ ሙሽራ እንክብካቤ ይፈልጋል " ያሉን አንድ የቡና ላኪ " በቦታዉ ባለዉ ወረፋ መብዛትና ተገቢነት በለሌዉ የተሽከርካሪ አቋቋም ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረግን ነዉ " ብለዋል።

" በማዕከሉ ዙሪያ ተሰልፈን አምስትና ስድስት ቀናትና አለፍ ሲልም ከዛም በላይ አስር ቀን የመቆየት ሁኔታዎች አሉ " ያሉን ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ የቡና አቅራቢ " ቡና ሳይወጋ በሻራ ዉስጥ ታፍኖ ለረጅም ቀናት ስለሚቆይ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በሚናቀርብበት ወቅት የጥራት ደረጃ መዉረድና በከፍተኛ ሁኔታ የኪሎግራም መቀነስ እያጋጠመን ነዉ " ብለዋል።

" ቀልጣፋ አገልግሎት ባለማግኘታችን በእኛና በተሽከርካሪ ባለቤቶች እንዲሁም በቡና አቅራቢዎች እና ጉዳይ አስፈፃሚዎች መካከል አለመተማመኖች እየተፈጠሩ ነዉ " ያሉን አሽከርካሪዎች " ለፓርኪንግ፣ ምግብ ፣ አልጋ መሰል አላስፈላጊ ወጪዎችን እያወጣን ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ቡና በሀገር ደረጃ ባለዉ ከፍተኛ የገቢ ምንጭነት ልክ ትኩረት አልተሰጠውም " የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ " ፈጣን መፍትሔ ካልተበጀለት ጉዳቱ ከኛ አልፎ አምራች አርሶአደሮች፣ ሰፊ የስራ ዕድል በተፈጠረላቸው ወጣቶችና በሀገር የዉጪ ምንዛሪ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ማሳደሩ አይቀርም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ስሜን አነጋግሯል።

እሳቸውም ፤ የዘንድሮ የቡና ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ቀደም ሲል ከነበረዉ የቦታ ጥበትና ተያያዥ ችግሮች ጋር ተዳምሮ ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ አለመሆን ዋነኛ ምክንያት መሆናቸዉን ተናግረዋል።

የችግሩን አሳሳብነትና የቡናን ሀገራዊ ጥቅሙን በመግለፅ ለሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ደብዳቤ መፃፋቸዉንና ምላሽም እየተጠባበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ መልኩ የቡና ምርቶች ወደ ማዕከሉ በሚደርሱበት ወቅት አስፈላጊዉ የእርጥበት መጠን ላይ ሳይደርሱ የሚመጡበት አጋጣሚዎች ስላሉ ተገቢዉ የእርጥበት መጠናቸዉ ላይ እስኪደርሱ ድረስ መወጋትም ሆነ የቅምሻ ልኬት ስለማይደረግላቸዉና ለኮንትሮባንድ እንዳይጋለጡ ሲባል ወደ ኋላ ስለማይመለሱ በማዕከሉ እንዲቆዩ ስለሚደረግ የተሽከርካሪዎች ክምችት እንደሚፋጠርም አስታውቀዋል።

ማዕከሉ ለሲዳማ፣ ለደቡብ ኢትዮጵያና ኦሮሚያ ክልል ቡና አምራች አከባቢዎች አገልግሎት የሚሰጥና የሀገራችንን ዋነኛ የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የሚያቀርብ እንደመሆኑ መጠን በተለይም የሲዳማ ክልል መንግስትና ተጠሪ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ መፍትሔ ቢሰጡ ጥሩ ነው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬን አነጋግሯል።

" ቡና ለሲዳማ ክልል ልዩ ትርጉም ያለዉ የገቢ ምንጭና የክልሉም መለያም ጭምር ነዉ " ያሉ ሲሆን በ2017 ዓ/ም ብቻ ከክልሉ ከ37 ሺ ቶን በላይ ቡና መሰብሰቡን ገልፀዉ በዘንድሮዉ ሀገር አቀፍ የቡና ቅምሻ ወድድር (ካፕ ኦፍ ኤክሰሌንስ) ከ1ኛ እስከ 39ኛ ድረስ የወጡት የክልሉ አምራች አርሶ አደሮች መሆናቸውን አስታዉቀዋል።

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ያለበትን ጫና የክልሉ መንግስት መረዳቱንና በአጭር ጊዜ ዉስጥ አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA









Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93774

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Ukrainian forces have since put up a strong resistance to the Russian troops amid the war that has left hundreds of Ukrainian civilians, including children, dead, according to the United Nations. Ukrainian and international officials have accused Russia of targeting civilian populations with shelling and bombardments. The channel appears to be part of the broader information war that has developed following Russia's invasion of Ukraine. The Kremlin has paid Russian TikTok influencers to push propaganda, according to a Vice News investigation, while ProPublica found that fake Russian fact check videos had been viewed over a million times on Telegram. There was another possible development: Reuters also reported that Ukraine said that Belarus could soon join the invasion of Ukraine. However, the AFP, citing a Pentagon official, said the U.S. hasn’t yet seen evidence that Belarusian troops are in Ukraine. Artem Kliuchnikov and his family fled Ukraine just days before the Russian invasion. Oh no. There’s a certain degree of myth-making around what exactly went on, so take everything that follows lightly. Telegram was originally launched as a side project by the Durov brothers, with Nikolai handling the coding and Pavel as CEO, while both were at VK.
from ms


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American