TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
“ ትላንት ‘ለምርመራ ትፈለጋለህ’ ተብሎ እንደተደወለለት አሳውቆን ነበር። ዛሬ ግን ከቤቱ ወስደው እንዳሰሩት ነው ቤተሰቦች ደውለው ያሳወቁን ” - ማኀበሩ
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዜዳንት የሆኑት አቶ ዮናታን ዳኛው “ በጸጥታ ኃይሎች ” ተወስደው ዛሬ መታሰራቸውን ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።
አቶ ዮናታን በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው የተወሰዱት ዛሬ መሆኑን የገለጸው ማኅበሩ “ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ” ሲል አሳስቧል።
“ የማኀበርን ፕሬዝዳንትና ሌሎች አመራሮችን በማሰርና በማገላታት ‘እርቦኛል’ ብሎ አደባባይ የወጣን የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ማፈን አይቻልም፣ ፕሬዝዳንቱን በአፋጣኝ በመፍታት የጤና ባለሙያዎችን ጥያቄ በአፋጣኝ መመለስ እንዳለበት ማህበሩ ያምናል ” ሲል አክሏል።
አቶ ዮናታን ዛሬ እንደተወሰዱ የገለጸው ማኀበሩ “ ከዛ በፊት ትላንት ‘ለምርመራ ትፈለጋለህ’ ተብሎ እንደተደወለለት አሳውቆ ነበር ዛሬ ግን ከቤቱ ወስደው እንዳሰሩት ነው ቤተሰቦች ደውለው ያሳወቁን ” ብሏል።
“ ጥያቄው አጠቃላይ የጤና ባለሙያ ሆኖ ሳለ ጥያቄው በውይይት እንዲፈታ ያሳሰቡ ግለሰቦችን ማፈን ተገቢ ነውን ? ነገ እኛም ምን እንደምንሆን አይታወቅምና መልክታችን ይህ ነው ” ሲል ገልጿል።
“ ፕሬዝዳንቱ የታሰረው ለግል ጉዳዩ አደለምና ማህበሩን በመወከል ከፍተኛ ድምፅ እየሆነ ለነበረው ፕሬዝዳንት አጋርነታችሁን አሳዩ ” ያለው የጤና ባለሙያዎች ማኅበሩ “ ሌሎች ጤና ባለሙያዎች ግለሰቦችን ማፈን የናንተን ረሃብ አያስቀረውምና ፍትሃዊ ጥያቄያችሁን ከፖለቲካ በጸዳ መልኩ እንድትቀጥሉ አበረታታለው ” ብሏል።
“ በቅዱስ ጳውሎስ፤ አርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሌሎች የተለያዬ አከባቢዎች ጤና ባለሙያዎች አፈናና ማዋከብ እየደረሰባቸው እንደሆነ እየሰማን ነው ” ሲልም ማኅበሩ ተናግሯል።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ባለፉት ሳምንታት “ የቆዩና ምላሽ ያላገኙ ” ያሏቸውን 12 ጥያቄዎች ለጤና ሚኒስቴር ጭምር በማቅረብ የጊዜ ገደብ ሰጥተው ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ እና ምላሽ ካላገኙ ወደ ቀጣይ እርምጃ እንደሚገቡ እየገለጹ ናቸው።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ከቀናት በፊት በሰጠን ቃል ፥ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ የዳቦ ጥያቄ መሆኑን በመግለጽ ሌላ መልክ ለማስያዝ፣ ወደሚፈልጉት አቅጣጫ ለመውሰድ፣ የፓለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሯሯጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቦ ነበር።
ባለሙያዎች የሚነሱትን የመብት ጥያቄዎች መንግሥት አድምጦ እንዲመልስላቸው ጥያቄዎቻቸው ምንም አይነት የፓለቲካ አጀንዳ እንደሌላቸው ፤ ከዚህ የባለሙያዎች ጥያቄ ጋር በተያያዘ ነገሩን የራሳቸው በማስመሰል የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክሩ አካላትም አርፈው እንዲቀመጡ ነበር ጥሪ ያቀርበው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዜዳንት የሆኑት አቶ ዮናታን ዳኛው “ በጸጥታ ኃይሎች ” ተወስደው ዛሬ መታሰራቸውን ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።
አቶ ዮናታን በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው የተወሰዱት ዛሬ መሆኑን የገለጸው ማኅበሩ “ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ” ሲል አሳስቧል።
“ የማኀበርን ፕሬዝዳንትና ሌሎች አመራሮችን በማሰርና በማገላታት ‘እርቦኛል’ ብሎ አደባባይ የወጣን የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ማፈን አይቻልም፣ ፕሬዝዳንቱን በአፋጣኝ በመፍታት የጤና ባለሙያዎችን ጥያቄ በአፋጣኝ መመለስ እንዳለበት ማህበሩ ያምናል ” ሲል አክሏል።
አቶ ዮናታን ዛሬ እንደተወሰዱ የገለጸው ማኀበሩ “ ከዛ በፊት ትላንት ‘ለምርመራ ትፈለጋለህ’ ተብሎ እንደተደወለለት አሳውቆ ነበር ዛሬ ግን ከቤቱ ወስደው እንዳሰሩት ነው ቤተሰቦች ደውለው ያሳወቁን ” ብሏል።
“ ጥያቄው አጠቃላይ የጤና ባለሙያ ሆኖ ሳለ ጥያቄው በውይይት እንዲፈታ ያሳሰቡ ግለሰቦችን ማፈን ተገቢ ነውን ? ነገ እኛም ምን እንደምንሆን አይታወቅምና መልክታችን ይህ ነው ” ሲል ገልጿል።
“ ፕሬዝዳንቱ የታሰረው ለግል ጉዳዩ አደለምና ማህበሩን በመወከል ከፍተኛ ድምፅ እየሆነ ለነበረው ፕሬዝዳንት አጋርነታችሁን አሳዩ ” ያለው የጤና ባለሙያዎች ማኅበሩ “ ሌሎች ጤና ባለሙያዎች ግለሰቦችን ማፈን የናንተን ረሃብ አያስቀረውምና ፍትሃዊ ጥያቄያችሁን ከፖለቲካ በጸዳ መልኩ እንድትቀጥሉ አበረታታለው ” ብሏል።
“ በቅዱስ ጳውሎስ፤ አርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሌሎች የተለያዬ አከባቢዎች ጤና ባለሙያዎች አፈናና ማዋከብ እየደረሰባቸው እንደሆነ እየሰማን ነው ” ሲልም ማኅበሩ ተናግሯል።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ባለፉት ሳምንታት “ የቆዩና ምላሽ ያላገኙ ” ያሏቸውን 12 ጥያቄዎች ለጤና ሚኒስቴር ጭምር በማቅረብ የጊዜ ገደብ ሰጥተው ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ እና ምላሽ ካላገኙ ወደ ቀጣይ እርምጃ እንደሚገቡ እየገለጹ ናቸው።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ከቀናት በፊት በሰጠን ቃል ፥ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ የዳቦ ጥያቄ መሆኑን በመግለጽ ሌላ መልክ ለማስያዝ፣ ወደሚፈልጉት አቅጣጫ ለመውሰድ፣ የፓለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሯሯጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቦ ነበር።
ባለሙያዎች የሚነሱትን የመብት ጥያቄዎች መንግሥት አድምጦ እንዲመልስላቸው ጥያቄዎቻቸው ምንም አይነት የፓለቲካ አጀንዳ እንደሌላቸው ፤ ከዚህ የባለሙያዎች ጥያቄ ጋር በተያያዘ ነገሩን የራሳቸው በማስመሰል የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክሩ አካላትም አርፈው እንዲቀመጡ ነበር ጥሪ ያቀርበው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😡2.26K😭290❤122🙏44😢32🕊26🥰13🤔13👏7😱5
group-telegram.com/tikvahethiopia/96670
Create:
Last Update:
Last Update:
“ ትላንት ‘ለምርመራ ትፈለጋለህ’ ተብሎ እንደተደወለለት አሳውቆን ነበር። ዛሬ ግን ከቤቱ ወስደው እንዳሰሩት ነው ቤተሰቦች ደውለው ያሳወቁን ” - ማኀበሩ
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዜዳንት የሆኑት አቶ ዮናታን ዳኛው “ በጸጥታ ኃይሎች ” ተወስደው ዛሬ መታሰራቸውን ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።
አቶ ዮናታን በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው የተወሰዱት ዛሬ መሆኑን የገለጸው ማኅበሩ “ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ” ሲል አሳስቧል።
“ የማኀበርን ፕሬዝዳንትና ሌሎች አመራሮችን በማሰርና በማገላታት ‘እርቦኛል’ ብሎ አደባባይ የወጣን የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ማፈን አይቻልም፣ ፕሬዝዳንቱን በአፋጣኝ በመፍታት የጤና ባለሙያዎችን ጥያቄ በአፋጣኝ መመለስ እንዳለበት ማህበሩ ያምናል ” ሲል አክሏል።
አቶ ዮናታን ዛሬ እንደተወሰዱ የገለጸው ማኀበሩ “ ከዛ በፊት ትላንት ‘ለምርመራ ትፈለጋለህ’ ተብሎ እንደተደወለለት አሳውቆ ነበር ዛሬ ግን ከቤቱ ወስደው እንዳሰሩት ነው ቤተሰቦች ደውለው ያሳወቁን ” ብሏል።
“ ጥያቄው አጠቃላይ የጤና ባለሙያ ሆኖ ሳለ ጥያቄው በውይይት እንዲፈታ ያሳሰቡ ግለሰቦችን ማፈን ተገቢ ነውን ? ነገ እኛም ምን እንደምንሆን አይታወቅምና መልክታችን ይህ ነው ” ሲል ገልጿል።
“ ፕሬዝዳንቱ የታሰረው ለግል ጉዳዩ አደለምና ማህበሩን በመወከል ከፍተኛ ድምፅ እየሆነ ለነበረው ፕሬዝዳንት አጋርነታችሁን አሳዩ ” ያለው የጤና ባለሙያዎች ማኅበሩ “ ሌሎች ጤና ባለሙያዎች ግለሰቦችን ማፈን የናንተን ረሃብ አያስቀረውምና ፍትሃዊ ጥያቄያችሁን ከፖለቲካ በጸዳ መልኩ እንድትቀጥሉ አበረታታለው ” ብሏል።
“ በቅዱስ ጳውሎስ፤ አርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሌሎች የተለያዬ አከባቢዎች ጤና ባለሙያዎች አፈናና ማዋከብ እየደረሰባቸው እንደሆነ እየሰማን ነው ” ሲልም ማኅበሩ ተናግሯል።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ባለፉት ሳምንታት “ የቆዩና ምላሽ ያላገኙ ” ያሏቸውን 12 ጥያቄዎች ለጤና ሚኒስቴር ጭምር በማቅረብ የጊዜ ገደብ ሰጥተው ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ እና ምላሽ ካላገኙ ወደ ቀጣይ እርምጃ እንደሚገቡ እየገለጹ ናቸው።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ከቀናት በፊት በሰጠን ቃል ፥ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ የዳቦ ጥያቄ መሆኑን በመግለጽ ሌላ መልክ ለማስያዝ፣ ወደሚፈልጉት አቅጣጫ ለመውሰድ፣ የፓለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሯሯጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቦ ነበር።
ባለሙያዎች የሚነሱትን የመብት ጥያቄዎች መንግሥት አድምጦ እንዲመልስላቸው ጥያቄዎቻቸው ምንም አይነት የፓለቲካ አጀንዳ እንደሌላቸው ፤ ከዚህ የባለሙያዎች ጥያቄ ጋር በተያያዘ ነገሩን የራሳቸው በማስመሰል የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክሩ አካላትም አርፈው እንዲቀመጡ ነበር ጥሪ ያቀርበው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዜዳንት የሆኑት አቶ ዮናታን ዳኛው “ በጸጥታ ኃይሎች ” ተወስደው ዛሬ መታሰራቸውን ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።
አቶ ዮናታን በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው የተወሰዱት ዛሬ መሆኑን የገለጸው ማኅበሩ “ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ” ሲል አሳስቧል።
“ የማኀበርን ፕሬዝዳንትና ሌሎች አመራሮችን በማሰርና በማገላታት ‘እርቦኛል’ ብሎ አደባባይ የወጣን የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ማፈን አይቻልም፣ ፕሬዝዳንቱን በአፋጣኝ በመፍታት የጤና ባለሙያዎችን ጥያቄ በአፋጣኝ መመለስ እንዳለበት ማህበሩ ያምናል ” ሲል አክሏል።
አቶ ዮናታን ዛሬ እንደተወሰዱ የገለጸው ማኀበሩ “ ከዛ በፊት ትላንት ‘ለምርመራ ትፈለጋለህ’ ተብሎ እንደተደወለለት አሳውቆ ነበር ዛሬ ግን ከቤቱ ወስደው እንዳሰሩት ነው ቤተሰቦች ደውለው ያሳወቁን ” ብሏል።
“ ጥያቄው አጠቃላይ የጤና ባለሙያ ሆኖ ሳለ ጥያቄው በውይይት እንዲፈታ ያሳሰቡ ግለሰቦችን ማፈን ተገቢ ነውን ? ነገ እኛም ምን እንደምንሆን አይታወቅምና መልክታችን ይህ ነው ” ሲል ገልጿል።
“ ፕሬዝዳንቱ የታሰረው ለግል ጉዳዩ አደለምና ማህበሩን በመወከል ከፍተኛ ድምፅ እየሆነ ለነበረው ፕሬዝዳንት አጋርነታችሁን አሳዩ ” ያለው የጤና ባለሙያዎች ማኅበሩ “ ሌሎች ጤና ባለሙያዎች ግለሰቦችን ማፈን የናንተን ረሃብ አያስቀረውምና ፍትሃዊ ጥያቄያችሁን ከፖለቲካ በጸዳ መልኩ እንድትቀጥሉ አበረታታለው ” ብሏል።
“ በቅዱስ ጳውሎስ፤ አርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሌሎች የተለያዬ አከባቢዎች ጤና ባለሙያዎች አፈናና ማዋከብ እየደረሰባቸው እንደሆነ እየሰማን ነው ” ሲልም ማኅበሩ ተናግሯል።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ባለፉት ሳምንታት “ የቆዩና ምላሽ ያላገኙ ” ያሏቸውን 12 ጥያቄዎች ለጤና ሚኒስቴር ጭምር በማቅረብ የጊዜ ገደብ ሰጥተው ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ እና ምላሽ ካላገኙ ወደ ቀጣይ እርምጃ እንደሚገቡ እየገለጹ ናቸው።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ከቀናት በፊት በሰጠን ቃል ፥ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ የዳቦ ጥያቄ መሆኑን በመግለጽ ሌላ መልክ ለማስያዝ፣ ወደሚፈልጉት አቅጣጫ ለመውሰድ፣ የፓለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሯሯጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቦ ነበር።
ባለሙያዎች የሚነሱትን የመብት ጥያቄዎች መንግሥት አድምጦ እንዲመልስላቸው ጥያቄዎቻቸው ምንም አይነት የፓለቲካ አጀንዳ እንደሌላቸው ፤ ከዚህ የባለሙያዎች ጥያቄ ጋር በተያያዘ ነገሩን የራሳቸው በማስመሰል የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሞክሩ አካላትም አርፈው እንዲቀመጡ ነበር ጥሪ ያቀርበው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA



Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/96670